ሀዋሳ ፤ግንቦት 8/2017 (ኢዜአ)፡- የተጎዳ መሬትን ተንከባክቦ በማልማትና መልሶ እንዲያገግም በማድረግ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየተደረጉ ያሉ ጥረቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆናቸውን የግብርና ሚኒስትሩ ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) አመለከቱ።
ሚኒስትሩን ጨምሮ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ እና የአጋር አካላት ተወካዮች በሲዳማ ክልል ያገገመ መሬት ያሉባቸው አካባቢዎችን ምልከታ አከናውነዋል።
የግብርና ሚኒስትሩ ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) በወቅቱ እንዳሉት የተራቆተ አካባቢን በማልማት የተለያየ ጠቀሜታ ያላቸው የፍራፍሬና የምግብ ተክሎችን አልምቶ ማህበረሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ እየተደረጉ ያሉ ጥረቶች ስኬት እያስመዘገቡ ነው።
ዛሬ ላይ ከአለም ባንክ ጋር በመተባበር በሲዳማ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች በተከናወኑ ተግባራት ተጎድቶ የነበረ መሬት አገግሞ ጥቅም ላይ ውሎ ማየታቸውን ጠቅሰው በዚህም መደሰታቸውን ገልጸዋል።
ለዚህም እንደማሳያ በሲዳማ ክልል ሸበዲኖ ወረዳ ለዓመታት ተራቁቶ የነዋሪው ስጋት የነበረውን አካባቢ ማህበረሰቡ ከልሎ በተፋሰስ በማልማት ቡና፣ አቦካዶ፣ እንሰትና ሌሎች ተክሎችን አልምቶ ገቢ እያገኘበት መሆኑን መመልከታቸውን ተናግረዋል።
የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ፤ የአለም ባንክ በውሀ፣ በአካባቢ ጥበቃና በተፋሰስ ልማት ዙሪያ በክልሉ የሚከናወኑ ተግባራትን እያገዘ ይገኛል ብለዋል።
በክልሉ በሚገኙ የተለያዩ ወረዳዎች 140 ሺህ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ ማድረግ ያስቻሉ 15 ፕሮጀክቶች ተቀርጸው ተግባራዊ እየተደረጉ እንደሚገኙና ለዚህ ማስፈጸሚያ የሚሆን 750 ሚሊዮን ብር በጀት እንደተመደበም ተናግረዋል።
የሲዳማ ክልል እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ማምሩ ሞኬ በበኩላቸው፥ በክልሉ 366 ተፋሰሶችን በመለየት 205 ሺህ ሄክታር የተራቆተ መሬት መልሶ እንዲያገግም መደረጉን ተናግረዋል።
በዚህም 51 ሺህ አባላት ያሉት ከ300 በላይ ማህበራትን በማደራጀት በንብ ማነብና በሌሎች መስኮች ተሰማርተው ጥበቃና እንክብካቤ በማድረግ ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በአለም ባንክ የምስራቅና ደቡባዊ አፍሪካ ሪጅናል ዳይሬክተር አና ዌለንስቲን እንዳሉት፥ የአለም ባንክ ከግብርናና ከውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በንጹህ ውሀ አቅርቦትና በተፈጥሮ ሀብት ልማትና አካባቢ ጥበቃ ዙሪያ የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል።
በሲዳማ ክልል በሸበዲኖ ወረዳ ለረጅም ዓመታት ተራቁቶ ለጎርፍ አደጋ ያጋልጥ የነበረን አካባቢ ነዋሪዎቹ አልምተው አቦካዶ በማልማትና ንብ በማነብ ስራ ተሰማርተው ኢኮኖሚያዊ አቅማቸውን ማሳደግ እንደቻሉ ማየታቸውን ተናግረዋል።
ዛሬ በሲዳማ ክልል አለታ ጩኮና ሸበዲኖ ወረዳዎች በአለም ባንክና አጋር አካላት ድጋፍ በተከናወኑ ተግባራት ምልከታ ላይ የግብርና ሚኒስቴርና የሲዳማ ክልል የስራ ኃላፊዎችና የአጋር አካላት ተወካዮች ተገኝተዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025
ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...
Feb 28, 2025
ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...
Feb 24, 2025