የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በዞኑ በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር እየተሳተፉ የሚገኙ ነዋሪዎች ተጠቃሚነታቸው እያደገ ነው

May 19, 2025

IDOPRESS

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 9/2017(ኢዜአ)፦ በምስራቅ ቦረና ዞን በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር እየተሳተፉ የሚገኙ ነዋሪዎች ተጠቃሚነታቸው እያደገ መሆኑን ገለጹ።

በዞኑ የሊበን ወረዳ ነዋሪ አቶ ኑራ ሀብቻና ከሦስት ጓደኞቻቸው ጋር በመሆን በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር በዶሮ እርባታ ስራ መሰማራታቸውን ገልጸዋል።

ባለፉት 6 ወራት ብቻ ከ6ሺህ በላይ የሥጋና የእንቁላል ዶሮዎችን በማርባት በየወሩ እስከ 3ሺህ እንቁላል ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ሥራ ሲጀምሩ የነበራቸው 100ሺህ ብር ካፒታል በዚህ ወቅት ከ400ሺህ ብር በማለፉ በቀጣይ ወደ ንብ ማነብና የወተት ላም እርባታ ለመሸጋገር እቅድ እንዳላቸው ገልጸዋል።


በነገሌ ቦረና ከተማ ዙሪያ ንብ በማናብ ሥራ የተሰማሩት አቶ ዘሪሁን በቀለ፤ 10 ዘመናዊ የንብ ቀፎ ተጠቅመው የንብ ማናብ ስራ መጀመራቸውን ጠቁመው ከ4ቱ ቀፎዎች ለመጀመሪያ ጊዜ 55 ኪሎ ግራም ማር ማግኘታቸውን ተናግረዋል፡፡

በተጨማሪም ማንጎ፣ ሙዝና ሌሎች የፍራፍሬ ችግኞችን ማልማት መጀመራቸውን ገልጸው የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ተጠቃሚ እያደረጋቸው መሆኑን አረጋግጠዋል።

የነገሌ ቦረና ከተማ ነዋሪውና በአሣ እርባታ ሥራ የተሰማሩት አቶ በሽር ዱባ፤ የአሳ ምርት ለገቢያ በማቅረብ ቤተሰቦቻቸውን እያስተዳደሩ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ወደ ፊትም ከአሣ እርባታ ስራ በሻገር በንብ ማነብ፣ በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት በመሳተፍ ገቢያቸውን ለማሳደግ ማቀደቻውን ጠቁመዋል።

በዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት የተፈጥሮ ጸጋዎች አጠቃቀም ባለሙያ አቶ በረከት ዳመነ እንዳሉት፤ በዞኑ በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ከ148 ሺህ በላይ ዜጎች እየተሳተፉ ነው።

በዚህም የአሳ ሀብት ልማት፣ የንብ፣ ዶሮ፣ የስጋና የወተት ላሞች እርባታ በስፋት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸው አትክልትና ፍራፍሬም እየተመረቱ መሆኑን ተናግረዋል።

የሌማት ትርፋት መርሃ ግብር ምርታማነትን ለማሳደግ ከ1 ሚሊዮን በላይ የዶሮ ጫጩቶዎች፣ ከ13 ሺህ በላይ ዘመናዊ የንብ ቀፎዎች ለተጠቃሚዎች መከፋፈላቸውን አስታውቀዋል።

በተለይም የተሰራጨው ዘመናዊ ቀፎ ቀድሞ ከአንድ ባህላዊ ቀፎ የሚገኘውን 8 ኪሎ ግራም የማር ምርት ወደ 35 ኪሎ ግራም ማሳደግ የሚያስችል ነው ብለዋል።

የሌማት ትሩፋት አምራቹንና ሸማቹን ተጠቃሚ ከማድረግ ባለፈ የምግብ ዋስትናን እያረጋገጠ መሆኑንም አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026