የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

ህብረተሰቡ ትውልድ ተሻጋሪ የመሰረተ ልማት ስራዎችን መጠበቅና መንከባከብ አለበት- የምክር ቤት አባላት

May 19, 2025

IDOPRESS

ባህር ዳር፤ግንቦት 10/2017 (ኢዜአ)፦በባህር ዳር ከተማ እየተገነቡ የሚገኙ ትውልድ ተሻጋሪ የመሰረተ ልማት ስራዎችን ህብረተሰቡ ሊጠብቃቸውና ሊንከባከባቸው ይገባል ሲሉ የከተማዋ አስተዳደር ምክር ቤት አባላት አሳሰቡ።

የምክር ቤት አባላቱ በከተማዋ የሚካሄደውን የኮሪደር ልማትን ጨምሮ በከተማዋ እየተገነቡ የሚገኙ የልማት ስራዎችን ተዘዋውረው ጐብኝተዋል።

የምክር ቤቱ አባል የሆኑት ሲስተር አዲስ ዓለም ካሴ በወቅቱ እንዳሉት፥ በከተማዋ እየተገነቡ ያሉ የልማት ስራዎች ትውልድ ተሻጋሪና የአመራር ቁርጠኝነትን በግልጽ የሚያንጸባርቁ ናቸው።

የከተማዋ አመራር የልማት ስራዎችን በጥራትና በስፋት ማከናወኑ ኃላፊነትን በአግባቡ ከተጠቀሙበት ህዝብን ለማገልገል ያለውን ዋጋ የሚያሳይ ነው ብለዋል።


ለዚህም በከተማዋ እየተገነቡ ያሉ የአረንጓዴ ልማት ስፍራዎች፣ የኮሪደር ልማት፣ የአስፋልት መንገዶችና ሌሎች የልማት ስራዎች ትልቅ ማሳያ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ግንባታዎቹ የባህር ዳር ከተማን ለቱሪስትና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ ለማድረግ የሚያስችሉ በመሆናቸው ነዋሪዎች የመንከባከብና የመጠበቅ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡም ድጋፍ ይደረጋል ብለዋል።

ሌላው የምክር ቤት አባል አቶ ዘላለም ጌታሁን በበኩላቸው፥ በከተማዋ እየተገነቡ ያሉ የአስፋልት መንገዶች የከተማዋን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የሚያፋጥኑ ናቸው ብለዋል።

ምክር ቤቱ በከተማዋ የሚከናወኑ የልማት ስራዎችን ክትትል እንደሚያደርግ ጠቁመው፥ ህብረተሰቡ የልማት ስራዎቹ ለረጅም ጊዜ አገልግሎት እንዲሰጡ መጠበቅና መንከባከብ ይጠበቅበታል ብለዋል።

የከተማዋ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው እንደገለጹት፥ የባህር ዳር ከተማን የኢኮኖሚና ቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ የሚያስችሉ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው።

ሰላምን ማጽናትና ዘላቂ ከማድረግ ጎን ለጎን የልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ጠቁመው፥ የልማት ስራዎቹ ተፈጥሮ የቸራትን የባህር ዳር ከተማ የበለጠ ውብ ለማድረግ የሚያስችሉ መሆናቸውንም ተናግረዋል።

ትናንት የተጀመረው የከተማ አስተዳደሩ ምክር ቤት 29 መደበኛ ጉባኤም ዛሬ እንደሚጠናቀቅ ታውቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025