
ባህር ዳር፤ግንቦት 10/2017 (ኢዜአ)፦በባህር ዳር ከተማ እየተገነቡ የሚገኙ ትውልድ ተሻጋሪ የመሰረተ ልማት ስራዎችን ህብረተሰቡ ሊጠብቃቸውና ሊንከባከባቸው ይገባል ሲሉ የከተማዋ አስተዳደር ምክር ቤት አባላት አሳሰቡ።
የምክር ቤት አባላቱ በከተማዋ የሚካሄደውን የኮሪደር ልማትን ጨምሮ በከተማዋ እየተገነቡ የሚገኙ የልማት ስራዎችን ተዘዋውረው ጐብኝተዋል።
የምክር ቤቱ አባል የሆኑት ሲስተር አዲስ ዓለም ካሴ በወቅቱ እንዳሉት፥ በከተማዋ እየተገነቡ ያሉ የልማት ስራዎች ትውልድ ተሻጋሪና የአመራር ቁርጠኝነትን በግልጽ የሚያንጸባርቁ ናቸው።
የከተማዋ አመራር የልማት ስራዎችን በጥራትና በስፋት ማከናወኑ ኃላፊነትን በአግባቡ ከተጠቀሙበት ህዝብን ለማገልገል ያለውን ዋጋ የሚያሳይ ነው ብለዋል።

ለዚህም በከተማዋ እየተገነቡ ያሉ የአረንጓዴ ልማት ስፍራዎች፣ የኮሪደር ልማት፣ የአስፋልት መንገዶችና ሌሎች የልማት ስራዎች ትልቅ ማሳያ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ግንባታዎቹ የባህር ዳር ከተማን ለቱሪስትና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ ለማድረግ የሚያስችሉ በመሆናቸው ነዋሪዎች የመንከባከብና የመጠበቅ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡም ድጋፍ ይደረጋል ብለዋል።
ሌላው የምክር ቤት አባል አቶ ዘላለም ጌታሁን በበኩላቸው፥ በከተማዋ እየተገነቡ ያሉ የአስፋልት መንገዶች የከተማዋን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የሚያፋጥኑ ናቸው ብለዋል።
ምክር ቤቱ በከተማዋ የሚከናወኑ የልማት ስራዎችን ክትትል እንደሚያደርግ ጠቁመው፥ ህብረተሰቡ የልማት ስራዎቹ ለረጅም ጊዜ አገልግሎት እንዲሰጡ መጠበቅና መንከባከብ ይጠበቅበታል ብለዋል።
የከተማዋ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው እንደገለጹት፥ የባህር ዳር ከተማን የኢኮኖሚና ቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ የሚያስችሉ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው።
ሰላምን ማጽናትና ዘላቂ ከማድረግ ጎን ለጎን የልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ጠቁመው፥ የልማት ስራዎቹ ተፈጥሮ የቸራትን የባህር ዳር ከተማ የበለጠ ውብ ለማድረግ የሚያስችሉ መሆናቸውንም ተናግረዋል።
ትናንት የተጀመረው የከተማ አስተዳደሩ ምክር ቤት 29 መደበኛ ጉባኤም ዛሬ እንደሚጠናቀቅ ታውቋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026