የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ዩኒቨርሲቲዎቹ በክልሉ የሚከናወኑ የልማት ስራዎችን በምርምር፣ ፈጠራና በማህበረሰብ አገልግሎት እያገዙ ነው

May 21, 2025

IDOPRESS

ወራቤ፤ ግንቦት 11/2017(ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች በክልሉ የሚከናወኑ የልማት ስራዎችን በምርምር፣ ፈጠራና በማህበረሰብ አገልግሎት እያገዙ መሆኑ ተገለጸ።

የወራቤ ዩኒቨርሲቲ 3ኛውን የምርምር ኮንፍረንስ “ፈጠራና ምርምር ለዘላቂ ልማትና ማህበራዊ ለውጥ” በሚል መሪ ሀሳብ እያካሄደ ነው።

የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ሀላፊ አቶ አንተነህ ፍቃዱ በኮንፍረንሱ እንዳሉት በክልሉ የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች የክልሉ መንግስት እያከናወነ ያለውን የልማት ስራ በምርምርና በአዳዲስ ፈጠራዎች የሚያግዙ ተግበራት እያከናወኑ ነው።

ክልሉን የሳይንስ፣ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ማዕከል በማድረግ ለኢኮኖሚ እድገት አስተዋጽኦ ማበርከት እንዲቻል እየተሰራ ነው ያሉት አቶ አንተነህ ለዚህ ደግሞ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ያላቸው ፋይዳ የጎላ መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህም በክልሉ የሚገኙት ወራቤ፣ ዋቸሞና ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲዎች የትምህርት ስብራትን ለመጠገን በክልሉ እየተካሄደ ያለውን ዘርፈ ብዙ ተግባራት እያገዙ መሆኑን አመልክተዋል።

በዚህም የመምህራንን አቅም በመገንባትና ለክልል አቀፍና ሀገር አቀፍ ፈተና ለሚወስዱ ተማሪዎች የማጠናከሪያ ትምህርት በመስጠትም አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑን ጠቅሰዋል።

የወራቤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ቶፊቅ ጀማል(ዶ/ር ኢ/ር) እንዳሉት ዩኒቨርሲቲው በመደበኛነት ከሚያከናውነው የመማር ማስተማር ስራ በተጓዳኝ የማህበረሰቡን ችግር የሚፈቱ ተግባራት ላይ እየተሳተፈ ይገኛል።

በግብርናው ዘርፍ የእንስሳትን ዝርያ በማሻሻልና ሀገር በቀል ዕውቀት ላይ በማተኮር የተለያዩ ተግባራት ማከናወኑንም ጠቅሰዋል።

በስልጤ ዞን ግጭትን ቀድሞ መከላከል በሚያስችለው “ሴራ” በተሰኘው የባህል ዕሴትን በጥናት በማስደገፍ ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ መተግበር የሚያስችሉ ስራዎች መሰራታቸውንም ተናግረዋል።

የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ፣ የምርምር፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርና የማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት አንዋር አህመድ በበኩላቸው በማህበረሰብ አገልግሎት የህዝብ መድሀኒት ቤት በመክፈት አገልግሎት እንዲሰጥ መደረጉን ተናግረዋል።

በትምህርቱ ዘርፍ አምና በክልሉ በ38 ትምህርት ቤቶች ለአስራ ሁለተኛ ክፍል ተማሪዎች የማጠናከሪያ ትምህርት በመስጠት ከሁለት አመት በፊት ከነበረው አንጻር የተማሪዎች ውጤት መሻሻል እንዲያሳይ ማገዙን ጠቁመዋል።

ዩኒቨርሲቲው በተያዘው ዓመትም ከ40 በሚበልጡ ትምህርት ቤቶች የማጠናከሪያ ትምህርት እየሰጠ እንደሚገኝም ገልጸዋል።

ዩኒቨርሲቲው ለሁለት ቀናት በሚያካሂደው 3ኛው የምርምር ኮንፍረንስ የተመረጡ 40 የምርምር ስራዎች ቀርበው ውይይት እንደሚደረግባቸው ተመላክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026