የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በክልሉ በውላቸው መሰረት የወርቅ ምርትን ለማዕከላዊ ገበያ በማያቀርቡ አምራቾችና አቅራቢዎች ላይ ህጋዊ እርምጃ ተወስዷል - ኤጀንሲው

May 21, 2025

IDOPRESS

ቦንጋ፤ ግንቦት 12/2017(ኢዜአ)፦ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በገቡት ውል መሰረት የወርቅ ምርትን ለማዕከላዊ ገበያ በማያቀርቡ አምራቾችና አቅራቢዎች ላይ ህጋዊ እርምጃ መውሰዱን የክልሉ ማዕድንና ኢነርጂ ልማት ኤጀንሲ አስታወቀ።

በበጀት ዓመቱ ባለፉት አስር ወራት ከ124 ኪሎ ግራም በላይ ወርቅ ከክልሉ ለብሔራዊ ባንክ መቅረቡም ተጠቁሟል።

የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር ገብረማሪያም ሰጠኝ፣ በክልሉ በርካታ የከበሩና ከፊል የከበሩ እንዲሁም ለግንባታ የሚያገለግሉ ማዕድናት እንዳሉ ገልጸው፣ ከእነዚህ መካከል ወርቅና የድንጋይ ከሰል በሰፊው እየተመረቱ ይገኛሉ ብለዋል።

በወርቅ ማምረት ሂደት ሥራ ፍቃድ ወስደው ወደ ሥራ የገቡ 85 የወርቅ አምራች ማህበራት እንዳሉም ጠቅሰዋል።

ከእነዚህ ማህበራት መካከል አብዛኞቹ በገቡት ውል መሠረት አምርተው ለገበያ አለማቅረባቸው ለብሔራዊ ባንክ የሚቀርብ የወርቅ ምርት አፈጻጸም እንዲያንስ ማድረጉንም አንስተዋል።

ችግሩን ለመፍታት በማህበራቱ ላይ ህጋዊና አስተዳደራዊ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን ገልጸው፣ ለአብነትም ለ36 ወርቅ አምራችና አቅራቢዎች የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ መሰጠቱን ጠቅሰዋል።

በተጨማሪም ለ24 ወርቅ አምራቾች ከባድ ማስጠንቀቂያ እንዲሁም የሰባት አምራች ማህበራት ፈቃድ እንዲሰረዝ ተደርጓል ብለዋል።

በቀሪ ወራት የተጠናከረ የድጋፍና ክትትል ሥራ በመስራት አፈጻጸሙን ለማሻሻል እንደሚሰራ አቶ ገብረማሪያም ገልጸዋል።

ማህበራቱ በተለይም የአካባቢ ጥበቃና ማህበራዊ ደህንነት ህግን አክብረው መልሶ የማልማት ሥራ እንዲሰሩ በተቀናጀ መልኩ ክትትልና ቁጥጥር እየተደረገ መሆኑንም አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢንዱስትሪ ፓርኩ መገንባት መንግሥት ለዘርፉ የሰጠውን ትኩረት በተጨባጭ ያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...

May 20, 2026

የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል 

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...

May 7, 2026

የከተማዋን ባህል፣ ታሪክ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በማልማት ለኢኮኖሚያዊ ጥቅም የማዋል ተግባራት ይጠናከራሉ

ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...

May 7, 2026

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026