የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በክልሉ በውላቸው መሰረት የወርቅ ምርትን ለማዕከላዊ ገበያ በማያቀርቡ አምራቾችና አቅራቢዎች ላይ ህጋዊ እርምጃ ተወስዷል - ኤጀንሲው

May 21, 2025

IDOPRESS

ቦንጋ፤ ግንቦት 12/2017(ኢዜአ)፦ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በገቡት ውል መሰረት የወርቅ ምርትን ለማዕከላዊ ገበያ በማያቀርቡ አምራቾችና አቅራቢዎች ላይ ህጋዊ እርምጃ መውሰዱን የክልሉ ማዕድንና ኢነርጂ ልማት ኤጀንሲ አስታወቀ።

በበጀት ዓመቱ ባለፉት አስር ወራት ከ124 ኪሎ ግራም በላይ ወርቅ ከክልሉ ለብሔራዊ ባንክ መቅረቡም ተጠቁሟል።

የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር ገብረማሪያም ሰጠኝ፣ በክልሉ በርካታ የከበሩና ከፊል የከበሩ እንዲሁም ለግንባታ የሚያገለግሉ ማዕድናት እንዳሉ ገልጸው፣ ከእነዚህ መካከል ወርቅና የድንጋይ ከሰል በሰፊው እየተመረቱ ይገኛሉ ብለዋል።

በወርቅ ማምረት ሂደት ሥራ ፍቃድ ወስደው ወደ ሥራ የገቡ 85 የወርቅ አምራች ማህበራት እንዳሉም ጠቅሰዋል።

ከእነዚህ ማህበራት መካከል አብዛኞቹ በገቡት ውል መሠረት አምርተው ለገበያ አለማቅረባቸው ለብሔራዊ ባንክ የሚቀርብ የወርቅ ምርት አፈጻጸም እንዲያንስ ማድረጉንም አንስተዋል።

ችግሩን ለመፍታት በማህበራቱ ላይ ህጋዊና አስተዳደራዊ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን ገልጸው፣ ለአብነትም ለ36 ወርቅ አምራችና አቅራቢዎች የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ መሰጠቱን ጠቅሰዋል።

በተጨማሪም ለ24 ወርቅ አምራቾች ከባድ ማስጠንቀቂያ እንዲሁም የሰባት አምራች ማህበራት ፈቃድ እንዲሰረዝ ተደርጓል ብለዋል።

በቀሪ ወራት የተጠናከረ የድጋፍና ክትትል ሥራ በመስራት አፈጻጸሙን ለማሻሻል እንደሚሰራ አቶ ገብረማሪያም ገልጸዋል።

ማህበራቱ በተለይም የአካባቢ ጥበቃና ማህበራዊ ደህንነት ህግን አክብረው መልሶ የማልማት ሥራ እንዲሰሩ በተቀናጀ መልኩ ክትትልና ቁጥጥር እየተደረገ መሆኑንም አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የአፍሪካ የልማትና ትብብር ዓርማ - ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በታዋቂው ታይም መጽሔት ገጽ

አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...

Sep 14, 2026

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026