
ቦንጋ፤ ግንቦት 12/2017(ኢዜአ)፦ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በገቡት ውል መሰረት የወርቅ ምርትን ለማዕከላዊ ገበያ በማያቀርቡ አምራቾችና አቅራቢዎች ላይ ህጋዊ እርምጃ መውሰዱን የክልሉ ማዕድንና ኢነርጂ ልማት ኤጀንሲ አስታወቀ።
በበጀት ዓመቱ ባለፉት አስር ወራት ከ124 ኪሎ ግራም በላይ ወርቅ ከክልሉ ለብሔራዊ ባንክ መቅረቡም ተጠቁሟል።
የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር ገብረማሪያም ሰጠኝ፣ በክልሉ በርካታ የከበሩና ከፊል የከበሩ እንዲሁም ለግንባታ የሚያገለግሉ ማዕድናት እንዳሉ ገልጸው፣ ከእነዚህ መካከል ወርቅና የድንጋይ ከሰል በሰፊው እየተመረቱ ይገኛሉ ብለዋል።
በወርቅ ማምረት ሂደት ሥራ ፍቃድ ወስደው ወደ ሥራ የገቡ 85 የወርቅ አምራች ማህበራት እንዳሉም ጠቅሰዋል።
ከእነዚህ ማህበራት መካከል አብዛኞቹ በገቡት ውል መሠረት አምርተው ለገበያ አለማቅረባቸው ለብሔራዊ ባንክ የሚቀርብ የወርቅ ምርት አፈጻጸም እንዲያንስ ማድረጉንም አንስተዋል።
ችግሩን ለመፍታት በማህበራቱ ላይ ህጋዊና አስተዳደራዊ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን ገልጸው፣ ለአብነትም ለ36 ወርቅ አምራችና አቅራቢዎች የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ መሰጠቱን ጠቅሰዋል።
በተጨማሪም ለ24 ወርቅ አምራቾች ከባድ ማስጠንቀቂያ እንዲሁም የሰባት አምራች ማህበራት ፈቃድ እንዲሰረዝ ተደርጓል ብለዋል።
በቀሪ ወራት የተጠናከረ የድጋፍና ክትትል ሥራ በመስራት አፈጻጸሙን ለማሻሻል እንደሚሰራ አቶ ገብረማሪያም ገልጸዋል።
ማህበራቱ በተለይም የአካባቢ ጥበቃና ማህበራዊ ደህንነት ህግን አክብረው መልሶ የማልማት ሥራ እንዲሰሩ በተቀናጀ መልኩ ክትትልና ቁጥጥር እየተደረገ መሆኑንም አስታውቀዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026