የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በብሔረሰብ አስተዳደሩ የሰብል ልማት ምርታማነትን ለማሳደግ የቅድመ ዝግጅት ስራ እያከናወነ ነው

May 26, 2025

IDOPRESS

ሰቆጣ፤ግንቦት 16/2017 (ኢዜአ) ፦የመኸር ወቅት የሰብል ልማት ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያስችሉ የዝግጅት ስራዎችን እያከናወኑ እንደሚገኙ በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር የጋዝጊብላ ወረዳ አርሶ አደሮች ገለፁ።


በብሔረሰብ አስተዳደሩ በ2017/18 የመኸር ወቅት 120 ሺህ 638 ሄክታር መሬት በዘር ለመሸፈን ታቅዶ እየተሰራ መሆኑ ተመላክቷል።


በጋዝጊብላ ወረዳ የመስቀሎ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት አርሶ አደር ፋንታው ምርኩዜ ለኢዜአ እንደገለፁት፥በመኸር ወቅቱ የስንዴ፤የገብስና የጤፍ ሰብሎችን ለማልማት አቅደው ዝግጅት እያደረጉ ይገኛሉ።


ከዚህ ውስጥም አንድ ሄክታር የእርሻ መሬትን በስንዴ ሰብል ለመሸፈን አቅደው ዝግጅት እያደረጉ መሆኑን ተናግረዋል።


ለዚህም አንደኛ ዙር እርሻ በማረስ ዝግጅት ማድረጋቸውን ጠቅሰው፥ የአፈር ማዳበሪያ በመጠቀም የዘር ስራውን ለማከናወን መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።


አርሶ አደር ባየ አበራ በበኩላቸው፥ግማሽ ሄክታር መሬት የስንዴ ሰብልን ጨምሮ ሌሎች ሰብሎችን ለማልማት የእርሻ ዝግጅት እያካሄዱ መሆናቸውን ተናግረዋል።


ስንዴን ከአካባቢው አርሶ አደሮች ጋር በመሆን በኩታ ገጠም ለመዝራት ዝግጅት እያደረጉ ሲሆን ለመኸር እርሻው የሚሆን ማዳበሪያ ከወዲሁ መቅረቡን ገልፀዋል።


በዚህም መሬቱን ደጋግሞ በማረስና በቂ ግብዓት በመጠቀም ምርታማነትን በሚያሳድግ አግባብ የሰብል ልማት ስራውን እያከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል።


በብሔረሰብ አስተዳደሩ በ2017/18 የመኸር ወቅት 120 ሺህ 638 ሄክታር መሬትን በተለያዩ ሰብሎች በዘር ለመሸፈን ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን የገለፁት ደግሞ የአስተዳደሩ የግብርና መምሪያ ሃላፊ አቶ አዲስ ወልዴ ናቸው።


የመኸር ሰብል ልማቱን ምርታማነት ለማሳደግም 32 ሺህ ኩንታል ማዳበሪያ ቀርቦ 12 ሺህ ያህሉ ለአርሶ አደሮች መሰራጨቱን ተናግረዋል።


በአስተዳደሩ የአካባቢን ፀጋ በመለየት ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው፥ በመኸር ወቅት እርሻው መታረስ ከሚችለው መሬት 110 ሺህ ሄክታር ያህሉ መሬት አንድ ዙር ታርሶ ለዘር ዝግጅት መደረጉን ገልፀዋል።


በብሔረሰብ አስተዳደሩ በ2017/18 የመኸር ወቅት ከሚለማው መሬት 1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢንዱስትሪ ፓርኩ መገንባት መንግሥት ለዘርፉ የሰጠውን ትኩረት በተጨባጭ ያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...

May 20, 2026

የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል 

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...

May 7, 2026

የከተማዋን ባህል፣ ታሪክ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በማልማት ለኢኮኖሚያዊ ጥቅም የማዋል ተግባራት ይጠናከራሉ

ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...

May 7, 2026

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026