
ሰቆጣ፤ግንቦት 16/2017 (ኢዜአ) ፦የመኸር ወቅት የሰብል ልማት ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያስችሉ የዝግጅት ስራዎችን እያከናወኑ እንደሚገኙ በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር የጋዝጊብላ ወረዳ አርሶ አደሮች ገለፁ።
በብሔረሰብ አስተዳደሩ በ2017/18 የመኸር ወቅት 120 ሺህ 638 ሄክታር መሬት በዘር ለመሸፈን ታቅዶ እየተሰራ መሆኑ ተመላክቷል።
በጋዝጊብላ ወረዳ የመስቀሎ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት አርሶ አደር ፋንታው ምርኩዜ ለኢዜአ እንደገለፁት፥በመኸር ወቅቱ የስንዴ፤የገብስና የጤፍ ሰብሎችን ለማልማት አቅደው ዝግጅት እያደረጉ ይገኛሉ።
ከዚህ ውስጥም አንድ ሄክታር የእርሻ መሬትን በስንዴ ሰብል ለመሸፈን አቅደው ዝግጅት እያደረጉ መሆኑን ተናግረዋል።
ለዚህም አንደኛ ዙር እርሻ በማረስ ዝግጅት ማድረጋቸውን ጠቅሰው፥ የአፈር ማዳበሪያ በመጠቀም የዘር ስራውን ለማከናወን መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።
አርሶ አደር ባየ አበራ በበኩላቸው፥ግማሽ ሄክታር መሬት የስንዴ ሰብልን ጨምሮ ሌሎች ሰብሎችን ለማልማት የእርሻ ዝግጅት እያካሄዱ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ስንዴን ከአካባቢው አርሶ አደሮች ጋር በመሆን በኩታ ገጠም ለመዝራት ዝግጅት እያደረጉ ሲሆን ለመኸር እርሻው የሚሆን ማዳበሪያ ከወዲሁ መቅረቡን ገልፀዋል።
በዚህም መሬቱን ደጋግሞ በማረስና በቂ ግብዓት በመጠቀም ምርታማነትን በሚያሳድግ አግባብ የሰብል ልማት ስራውን እያከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል።
በብሔረሰብ አስተዳደሩ በ2017/18 የመኸር ወቅት 120 ሺህ 638 ሄክታር መሬትን በተለያዩ ሰብሎች በዘር ለመሸፈን ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን የገለፁት ደግሞ የአስተዳደሩ የግብርና መምሪያ ሃላፊ አቶ አዲስ ወልዴ ናቸው።
የመኸር ሰብል ልማቱን ምርታማነት ለማሳደግም 32 ሺህ ኩንታል ማዳበሪያ ቀርቦ 12 ሺህ ያህሉ ለአርሶ አደሮች መሰራጨቱን ተናግረዋል።
በአስተዳደሩ የአካባቢን ፀጋ በመለየት ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው፥ በመኸር ወቅት እርሻው መታረስ ከሚችለው መሬት 110 ሺህ ሄክታር ያህሉ መሬት አንድ ዙር ታርሶ ለዘር ዝግጅት መደረጉን ገልፀዋል።
በብሔረሰብ አስተዳደሩ በ2017/18 የመኸር ወቅት ከሚለማው መሬት 1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026