ገንዳ ውሃ፤ግንቦት 16/20217 (ኢዜአ)፦በአካባቢው የሰፈነውን ሰላም በመጠበቅ በግብርናው ዘርፍ የተጀመሩ የኢንቨስትመንት ስራዎችን አጠናክረው እንደሚያስቀጥሉ በምእራብ ጎንደር ዞን በእርሻ ኢንቨስትመንት ላይ የተሰማሩ ባለሃብቶችና አርሶ አደሮች ገለጹ።
በምዕራብ ጎንደር ዞን መተማ ወረዳ በእርሻ ኢንቨስትመንት ላይ ከተሰማሩ ባለሃብቶችና አርሶ አደሮች ጋር የምክክር መድረክ ዛሬ ተካሄዷል።
በመተማ ወረዳ ከዳስጉንዶ ቀበሌ የመጡት አርሶ አደር ሰኢድ ሙሀመድ በምክክሩ ላይ እንደገለጹት በአካባቢው የተፈጠረው የጸጥታ ችግር በልማትና መልካም አስተዳደር ስራዎች ላይ እንቅፋት ሆኗል።
ሆኖም አሁን ላይ በአካባቢው በሰፈነው ሰላም ምክንያትም የጀመሩትን የልማት ስራ ለማስቀጠል እየሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ከመተማ ዮሃንስ ከተማ አስተዳደር የመጡት ባለሃብት አቶ ደሴ ሲሳይ በበኩላቸው በአካባቢው የሰፈነው ሰላም ወደ ልማት ለመግባት አመቺ መሆኑን ገልፀው የአካባቢውን ሰላም በማስጠበቅ ረገድም የድርሻቸውን እንደሚወጡ ገልጸዋል።
በእርሻ ኢንቨስትመንት ረገድ ያጋጠሙ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ከመንግስት ጎን በመቆም ለመፍታት የሚጠበቅባቸውን ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
ከመንግስት ጋር በመሆን በአካባቢው የሰፈነውን ሰላም በመጠበቅና የህግ የበላይነት ስራዎች እንዲጠናከሩ አበክረው እንደሚሰሩ የገለፁት ደግሞ ሌላኛው ባለሃብት አቶ ሙሀመድ ካቲም ናቸው።
በሰላም ረገድ የተፈጠረውን ዕድል በመጠበቅ የጀመሩትን የእርሻ ኢንቨስትመንት ስራ ለማስቀጠል የተለያዩ ተግባራትን እያከናወኑ መሆኑንም አክለዋል።
የአማራ ክልል ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ባለስልጣን ኃላፊ አቶ ዘውዱ ማለደ እንደገለጹት መንግስት በክልሉ ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን እየሰራ ይገኛል።
አካባቢው ሰፊ የእርሻ ኢንቨስትመንት የሚካሄድበት የልማት ቀጠና ቢሆንም ባጋጠመ ወቅታዊ ምክንያት በስፊው መልማት አለመቻሉን ገልፀው ''ለሰላም መስፈን ቅድሚያ ሰጥተን ልንሰራ ይገባል'' ብለዋል።
በአካባቢው የህግ የበላይነትን ከማስከበር ጎን ለጎን በአርሶ አደሩና በባለሃብቱ የሚነሱ መልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት ክልሉ ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረዋል።
የዞኑ ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አንዳርጌ ጌጡ በበኩላቸው አሁን ላይ የተገኘው ሰላም ከባለሃብቱና ከአርሶ አደሩ ጋር መነጋገር የሚያስችል እድል መፍጠሩን አስረድተዋል።
በቀጣይም መንግስት እያደረገ ያለውን የህግ ማስከበር ተግባር አጠናክሮ የሚቀጥል ሲሆን ህዝቡም የፅንፈኝነት አስተሳሰብን በመቃወም የትግሉ አካል መሆን እንዳለበትም አሳስበዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025
ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...
Feb 28, 2025
ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...
Feb 24, 2025