
ጎንደር፤ግንቦት 19/2017 (ኢዜአ)፦በማእከላዊ ጎንደር ዞን ከ240 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ እየተገነቡ ካሉት የመስኖ ፕሮጀክቶች መካከል ስድስቱ ተጠናቀው ለአገልግሎት ክፍት መሆናቸውን የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች መምሪያ አስታወቀ፡፡
የመምሪያው ተወካይ ኃላፊ አቶ ተስፋሁን ፈለቀ ለኢዜአ እንደገለጹት፥ የመስኖ ፕሮጀክቶችን በመገንባት አርሶ አደሩ በመስኖ ጭምር ተጠቅሞ በምግብ ራሱን እንዲችል እየተሰራ ነው።
በዚህም በዞኑ የሰፈነው ሰላም የፈጠረውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም በበጀት ዓመቱ ከተጀመሩ 26 የመስኖ ፕሮጀክቶች ውስጥ አሁን ላይ ስድስቱን በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ማብቃት መቻሉን ገልጸዋል።
የተጠናቀቁት የመስኖ ፕሮጀክቶችም ከሁለት ሺህ በላይ አርሶ አደሮችን በማሳተፍ ከ500 ሄክታር በላይ መሬትን በማልማት ከራሳቸው አልፎ ለገበያ የሚተርፍ ምርት ለማምረት የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል።
በመንግስትና መንግስታዊ ባልሆኑ ድርጅቶችና በህብረተሰቡ ተሳትፎ የተገነቡት ፕሮጀክቶች ከ1 ሺህ 300 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ እድል መፍጠር መቻሉን ገልጸዋል፡፡
በዝናብ አጠር አካባቢዎች የተገነቡት የመስኖ ፕሮጀክቶች የአርሶ አደሩን የምግብ ሉዓላዊነት የሚያረጋግጡና በምግብ ሰብል ምርት ራስን ለመቻል ለሚደረገው እንቅስቃሴ ምቹ መደላድልን የሚፈጥሩ ናቸው ብለዋል፡፡
ቀሪዎቹን ፕሮጀክቶች ፈጥኖ በማጠናቀቅ በቀጣዩ ዓመት ወደ ስራ ለማስገባት እየተሰራ እንደሚገኝም አቶ ተስፋሁን አስረድተዋል።
የአርሶ አደሩን ኑሮና ህይወት ለመቀየር የሚያግዙ የመስኖ ፕሮጀክቶች ደጃፋችን ላይ ተገንብተው በዓመት ሁለቴ አምርተን ለመጠቀም ችለናል ያሉት የምእራብ ደንቢያ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር የሻምበል የኋላሸት ናቸው፡፡
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026