
ጎንደር፤ግንቦት 19/2017 (ኢዜአ)፦በማእከላዊ ጎንደር ዞን ከ240 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ እየተገነቡ ካሉት የመስኖ ፕሮጀክቶች መካከል ስድስቱ ተጠናቀው ለአገልግሎት ክፍት መሆናቸውን የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች መምሪያ አስታወቀ፡፡
የመምሪያው ተወካይ ኃላፊ አቶ ተስፋሁን ፈለቀ ለኢዜአ እንደገለጹት፥ የመስኖ ፕሮጀክቶችን በመገንባት አርሶ አደሩ በመስኖ ጭምር ተጠቅሞ በምግብ ራሱን እንዲችል እየተሰራ ነው።
በዚህም በዞኑ የሰፈነው ሰላም የፈጠረውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም በበጀት ዓመቱ ከተጀመሩ 26 የመስኖ ፕሮጀክቶች ውስጥ አሁን ላይ ስድስቱን በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ማብቃት መቻሉን ገልጸዋል።
የተጠናቀቁት የመስኖ ፕሮጀክቶችም ከሁለት ሺህ በላይ አርሶ አደሮችን በማሳተፍ ከ500 ሄክታር በላይ መሬትን በማልማት ከራሳቸው አልፎ ለገበያ የሚተርፍ ምርት ለማምረት የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል።
በመንግስትና መንግስታዊ ባልሆኑ ድርጅቶችና በህብረተሰቡ ተሳትፎ የተገነቡት ፕሮጀክቶች ከ1 ሺህ 300 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ እድል መፍጠር መቻሉን ገልጸዋል፡፡
በዝናብ አጠር አካባቢዎች የተገነቡት የመስኖ ፕሮጀክቶች የአርሶ አደሩን የምግብ ሉዓላዊነት የሚያረጋግጡና በምግብ ሰብል ምርት ራስን ለመቻል ለሚደረገው እንቅስቃሴ ምቹ መደላድልን የሚፈጥሩ ናቸው ብለዋል፡፡
ቀሪዎቹን ፕሮጀክቶች ፈጥኖ በማጠናቀቅ በቀጣዩ ዓመት ወደ ስራ ለማስገባት እየተሰራ እንደሚገኝም አቶ ተስፋሁን አስረድተዋል።
የአርሶ አደሩን ኑሮና ህይወት ለመቀየር የሚያግዙ የመስኖ ፕሮጀክቶች ደጃፋችን ላይ ተገንብተው በዓመት ሁለቴ አምርተን ለመጠቀም ችለናል ያሉት የምእራብ ደንቢያ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር የሻምበል የኋላሸት ናቸው፡፡
አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...
Sep 14, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026