የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በማእከላዊ ጎንደር ዞን ከሚገነቡ የመስኖ ፕሮጀክቶች መካከል ስድስቱ ተጠናቀው ለአገልግሎት ክፍት ሆኑ

May 28, 2025

IDOPRESS

ጎንደር፤ግንቦት 19/2017 (ኢዜአ)፦በማእከላዊ ጎንደር ዞን ከ240 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ እየተገነቡ ካሉት የመስኖ ፕሮጀክቶች መካከል ስድስቱ ተጠናቀው ለአገልግሎት ክፍት መሆናቸውን የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች መምሪያ አስታወቀ፡፡


የመምሪያው ተወካይ ኃላፊ አቶ ተስፋሁን ፈለቀ ለኢዜአ እንደገለጹት፥ የመስኖ ፕሮጀክቶችን በመገንባት አርሶ አደሩ በመስኖ ጭምር ተጠቅሞ በምግብ ራሱን እንዲችል እየተሰራ ነው።


በዚህም በዞኑ የሰፈነው ሰላም የፈጠረውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም በበጀት ዓመቱ ከተጀመሩ 26 የመስኖ ፕሮጀክቶች ውስጥ አሁን ላይ ስድስቱን በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ማብቃት መቻሉን ገልጸዋል።


የተጠናቀቁት የመስኖ ፕሮጀክቶችም ከሁለት ሺህ በላይ አርሶ አደሮችን በማሳተፍ ከ500 ሄክታር በላይ መሬትን በማልማት ከራሳቸው አልፎ ለገበያ የሚተርፍ ምርት ለማምረት የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል።


በመንግስትና መንግስታዊ ባልሆኑ ድርጅቶችና በህብረተሰቡ ተሳትፎ የተገነቡት ፕሮጀክቶች ከ1 ሺህ 300 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ እድል መፍጠር መቻሉን ገልጸዋል፡፡


በዝናብ አጠር አካባቢዎች የተገነቡት የመስኖ ፕሮጀክቶች የአርሶ አደሩን የምግብ ሉዓላዊነት የሚያረጋግጡና በምግብ ሰብል ምርት ራስን ለመቻል ለሚደረገው እንቅስቃሴ ምቹ መደላድልን የሚፈጥሩ ናቸው ብለዋል፡፡


ቀሪዎቹን ፕሮጀክቶች ፈጥኖ በማጠናቀቅ በቀጣዩ ዓመት ወደ ስራ ለማስገባት እየተሰራ እንደሚገኝም አቶ ተስፋሁን አስረድተዋል።


የአርሶ አደሩን ኑሮና ህይወት ለመቀየር የሚያግዙ የመስኖ ፕሮጀክቶች ደጃፋችን ላይ ተገንብተው በዓመት ሁለቴ አምርተን ለመጠቀም ችለናል ያሉት የምእራብ ደንቢያ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር የሻምበል የኋላሸት ናቸው፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢንዱስትሪ ፓርኩ መገንባት መንግሥት ለዘርፉ የሰጠውን ትኩረት በተጨባጭ ያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...

May 20, 2026

የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል 

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...

May 7, 2026

የከተማዋን ባህል፣ ታሪክ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በማልማት ለኢኮኖሚያዊ ጥቅም የማዋል ተግባራት ይጠናከራሉ

ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...

May 7, 2026

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026