
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የአፍሪካ የወደፊት የኢንዱስትሪ ማዕከል መሆን የሚስችላትን መሠረት እየገነባች መሆኑን አሜሪካዊው የአፍሪካ ፖለቲካና ኢኮኖሚ ጉዳዮች ተንታኝ ላውረንስ ፍሪማን ገለጹ፡፡
ተንታኙ በኢትዮጵያ የሚገኙ የጨርቃጨርቅና አልባሳት፣ የብረታ ብረትና የስኳር ፋብሪካዎችንና ሌሎች የማምረቻ ኢንዱስትሪዎችን ጎብኝተዋል፡፡
በዚህም ኢትዮጵያ በአምራች ዘርፉ ዕድገት እያስመዘገበች መሆኗን መመልከታቸውን ተናግረዋል፡፡
ኢትዮጵያ እንደ ጨርቃጨርቅ ኢንዱስትሪ ያሉ በርካታ የማኑፋክቸሪንግ ስራዎች እንዳሏት ያነሱት ተንታኙ በዘርፉ የጀመረችውን ሽግግር ይበልጥ ማፋጠን እንዳለባትም ገልጸዋል፡፡

የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ለማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ ዕድገት ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው፤ በዚህም ኢትዮጵያ የአፍሪካ የወደፊት የኢንዱስትሪ ማዕከል መሆን የሚስችላትን መሠረት እየገነባች ነው ብለዋል፡፡
የአፍሪካ ፖለቲካና ኢኮኖሚ ጉዳዮች ተንታኙ አክለውም ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ በማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ የስራ ዕድል የተፈጠረላቸው ዜጎች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን ተመልክቻለሁ ነው ያሉት፡፡
እንደ አሜሪካ ያሉ ሀገራት ለማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ትልቅ ትኩረት በመስጠት ዛሬ ያሉበት ደረጃ ላይ መድረሳቸውን ጠቁመው፤ በኢትዮጵያ በአምራች ዘርፉ እየተከናወኑ በሚገኙ ስራዎች መደሰታቸውን ተናግረዋል፡፡
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026