አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የአፍሪካ የወደፊት የኢንዱስትሪ ማዕከል መሆን የሚስችላትን መሠረት እየገነባች መሆኑን አሜሪካዊው የአፍሪካ ፖለቲካና ኢኮኖሚ ጉዳዮች ተንታኝ ላውረንስ ፍሪማን ገለጹ፡፡
ተንታኙ በኢትዮጵያ የሚገኙ የጨርቃጨርቅና አልባሳት፣ የብረታ ብረትና የስኳር ፋብሪካዎችንና ሌሎች የማምረቻ ኢንዱስትሪዎችን ጎብኝተዋል፡፡
በዚህም ኢትዮጵያ በአምራች ዘርፉ ዕድገት እያስመዘገበች መሆኗን መመልከታቸውን ተናግረዋል፡፡
ኢትዮጵያ እንደ ጨርቃጨርቅ ኢንዱስትሪ ያሉ በርካታ የማኑፋክቸሪንግ ስራዎች እንዳሏት ያነሱት ተንታኙ በዘርፉ የጀመረችውን ሽግግር ይበልጥ ማፋጠን እንዳለባትም ገልጸዋል፡፡
የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ለማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ ዕድገት ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው፤ በዚህም ኢትዮጵያ የአፍሪካ የወደፊት የኢንዱስትሪ ማዕከል መሆን የሚስችላትን መሠረት እየገነባች ነው ብለዋል፡፡
የአፍሪካ ፖለቲካና ኢኮኖሚ ጉዳዮች ተንታኙ አክለውም ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ በማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ የስራ ዕድል የተፈጠረላቸው ዜጎች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን ተመልክቻለሁ ነው ያሉት፡፡
እንደ አሜሪካ ያሉ ሀገራት ለማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ትልቅ ትኩረት በመስጠት ዛሬ ያሉበት ደረጃ ላይ መድረሳቸውን ጠቁመው፤ በኢትዮጵያ በአምራች ዘርፉ እየተከናወኑ በሚገኙ ስራዎች መደሰታቸውን ተናግረዋል፡፡
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025
ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...
Feb 28, 2025
ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...
Feb 24, 2025