የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ኢትዮጵያ የአፍሪካ የወደፊት የኢንዱስትሪ ማዕከል መሆን የሚስችላትን መሠረት እየገነባች ነው - የአፍሪካ ፖለቲካና ኢኮኖሚ ጉዳዮች ተንታኝ ላውረንስ ፍሪማን

May 28, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የአፍሪካ የወደፊት የኢንዱስትሪ ማዕከል መሆን የሚስችላትን መሠረት እየገነባች መሆኑን አሜሪካዊው የአፍሪካ ፖለቲካና ኢኮኖሚ ጉዳዮች ተንታኝ ላውረንስ ፍሪማን ገለጹ፡፡

ተንታኙ በኢትዮጵያ የሚገኙ የጨርቃጨርቅና አልባሳት፣ የብረታ ብረትና የስኳር ፋብሪካዎችንና ሌሎች የማምረቻ ኢንዱስትሪዎችን ጎብኝተዋል፡፡

በዚህም ኢትዮጵያ በአምራች ዘርፉ ዕድገት እያስመዘገበች መሆኗን መመልከታቸውን ተናግረዋል፡፡

ኢትዮጵያ እንደ ጨርቃጨርቅ ኢንዱስትሪ ያሉ በርካታ የማኑፋክቸሪንግ ስራዎች እንዳሏት ያነሱት ተንታኙ በዘርፉ የጀመረችውን ሽግግር ይበልጥ ማፋጠን እንዳለባትም ገልጸዋል፡፡


የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ለማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ ዕድገት ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው፤ በዚህም ኢትዮጵያ የአፍሪካ የወደፊት የኢንዱስትሪ ማዕከል መሆን የሚስችላትን መሠረት እየገነባች ነው ብለዋል፡፡

የአፍሪካ ፖለቲካና ኢኮኖሚ ጉዳዮች ተንታኙ አክለውም ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ በማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ የስራ ዕድል የተፈጠረላቸው ዜጎች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን ተመልክቻለሁ ነው ያሉት፡፡

እንደ አሜሪካ ያሉ ሀገራት ለማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ትልቅ ትኩረት በመስጠት ዛሬ ያሉበት ደረጃ ላይ መድረሳቸውን ጠቁመው፤ በኢትዮጵያ በአምራች ዘርፉ እየተከናወኑ በሚገኙ ስራዎች መደሰታቸውን ተናግረዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢንዱስትሪ ፓርኩ መገንባት መንግሥት ለዘርፉ የሰጠውን ትኩረት በተጨባጭ ያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...

May 20, 2026

የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል 

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...

May 7, 2026

የከተማዋን ባህል፣ ታሪክ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በማልማት ለኢኮኖሚያዊ ጥቅም የማዋል ተግባራት ይጠናከራሉ

ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...

May 7, 2026

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026