የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ኢትዮጵያ የአፍሪካ የወደፊት የኢንዱስትሪ ማዕከል መሆን የሚስችላትን መሠረት እየገነባች ነው - የአፍሪካ ፖለቲካና ኢኮኖሚ ጉዳዮች ተንታኝ ላውረንስ ፍሪማን

May 28, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የአፍሪካ የወደፊት የኢንዱስትሪ ማዕከል መሆን የሚስችላትን መሠረት እየገነባች መሆኑን አሜሪካዊው የአፍሪካ ፖለቲካና ኢኮኖሚ ጉዳዮች ተንታኝ ላውረንስ ፍሪማን ገለጹ፡፡

ተንታኙ በኢትዮጵያ የሚገኙ የጨርቃጨርቅና አልባሳት፣ የብረታ ብረትና የስኳር ፋብሪካዎችንና ሌሎች የማምረቻ ኢንዱስትሪዎችን ጎብኝተዋል፡፡

በዚህም ኢትዮጵያ በአምራች ዘርፉ ዕድገት እያስመዘገበች መሆኗን መመልከታቸውን ተናግረዋል፡፡

ኢትዮጵያ እንደ ጨርቃጨርቅ ኢንዱስትሪ ያሉ በርካታ የማኑፋክቸሪንግ ስራዎች እንዳሏት ያነሱት ተንታኙ በዘርፉ የጀመረችውን ሽግግር ይበልጥ ማፋጠን እንዳለባትም ገልጸዋል፡፡


የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ለማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ ዕድገት ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው፤ በዚህም ኢትዮጵያ የአፍሪካ የወደፊት የኢንዱስትሪ ማዕከል መሆን የሚስችላትን መሠረት እየገነባች ነው ብለዋል፡፡

የአፍሪካ ፖለቲካና ኢኮኖሚ ጉዳዮች ተንታኙ አክለውም ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ በማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ የስራ ዕድል የተፈጠረላቸው ዜጎች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን ተመልክቻለሁ ነው ያሉት፡፡

እንደ አሜሪካ ያሉ ሀገራት ለማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ትልቅ ትኩረት በመስጠት ዛሬ ያሉበት ደረጃ ላይ መድረሳቸውን ጠቁመው፤ በኢትዮጵያ በአምራች ዘርፉ እየተከናወኑ በሚገኙ ስራዎች መደሰታቸውን ተናግረዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026