ጂንካ፤ግንቦት 21/2017(ኢዜአ)፦በጂንካ ከተማ በመጀመሪያው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት የመዝናኛ ፓርክን ጨምሮ 2 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ስራ መከናወኑን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ ።
የጂንካ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ስራ አስኪያጅ አቶ አሳየኝ በቀለ ለኢዜአ እንዳሉት፤ በከተማው ነዋሪውን ያሳተፈ የኮሪደር ልማት ስራ 2 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ስራ ተከናውኗል።
''ጂንካን በጋራ እናልማ ''በሚል መሪ ሃሳብ በተካሄደ ህዝባዊ ንቅናቄ ለኮሪደር ልማቱ ከ70 ሚሊዮን ብር በላይ ሀብት መሰብሰቡን ገልፀዋል።
በዚህም የጂንካ ከተማን ገጽታ በመቀየር ሳቢና ምቹ ሊያደርጋት የሚችል የተቀናጀ የኮሪደር ልማት መሰራቱን ጠቅሰዋል።
ከተሰሩ ስራዎች መካከል ለበአላት ማክበሪያ እንዲሁም ለመዝናኛ አገልግሎት የሚውል ፓርክ፣ የእግረኛ መንገድ፣ የመንገድ አካፋይ፣ የመብራት ዝርጋታና የአደባባይ ልማትን ለአብነት አንስተዋል።
የመንገድ ዳርቻ የአረንጓዴ ልማት ስራዎችን ጨምሮ 2 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ስራ ተጠናቅቆ አገልግሎት በመስጠት ላይ መሆኑን ጠቅሰው፥ ልማቱ ለከተማዋ ልዩ ገጽታን ማላበሱን ተናግረዋል።
የከተማው ነዋሪ ልማቱን ለማሳለጥ የሚያደርገው አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑን አንስተው፥ የከተማ አስተዳደሩም ይህን አቅም በመጠቀም የበለጠ ለማልማት እየሰራ መሆኑን አስረድተዋል።
በቀጣይም በሁለተኛው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ሦስት ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ስራ ለማከናወን መታቀዱን አመልክተዋል።
በከተማዋ የተጀመረው የኮሪደር ልማት ለከተማ ዕድገት ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን የተናገሩት የከተማዋ ነዋሪ አቶ ከሊል ሙሐመድ፥ ዘገምተኛ ለነበረው የከተማዋ ዕድገት መፋጠን ትልቅ ዕድል ይዞ የመጣ ነው ብለዋል።
በከተማዋ የተጀመረው የኮሪደር ልማት ስራ የከተማዋን እድገት አንድ እርምጃ ከፍ አድርጎታል ያሉት ደግሞ ወይዘሮ ትዕግሥት አድማሱ ናቸው።
ከዚህ ቀደም በቂ የእግረኛ መንገድ ባለመኖሩ የተሽከርካሪ አደጋ በስፋት ይከሰት እንደነበር አስታውሰው።
አሁን ላይ የእግረኛ መንገዶች ከተሰሩ በኃላ የተሽከርካሪ አደጋ መቀነሱን አንስተው፥ ከተማዋም ውብ፣ፅዱና ማራኪ እየሆነች መምጣቷን ተናግረዋል።
በከተማዋ የተጀመረው ልማት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ጠቅሰው፥ እየተከናወነ ያለውን ተግባር በመደገፍ ረገድ የሚጠበቅባቸውን ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025
ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...
Feb 28, 2025
ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...
Feb 24, 2025