ባህርዳር፤ ግንቦት 23/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል በመምህራንና ተማሪዎች የሚከናወኑ የፈጠራ ስራዎችን በማበረታታት ልማት ላይ እንዲውሉ እየተመቻቸ መሆኑን የክልሉ ትምህርት ቢሮ ገለጸ።
"ፈጠራ ለሁለንተናዊ ብልፅግና" በሚል መሪ ሃሳብ ትምህርት ቢሮው ያዘጋጀው የተማሪዎችና የመምህራን ክልላዊ የሳይንስ ፈጠራ ስራዎች አውደ ርዕይ ዛሬ ተመርቆ ለዕይታ ቀርቧል።
በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮው ኃላፊ ሙሉነሽ ደሴ(ዶ/ር) እንዳሉት፤ የሀገራት ዕድገት የሚለካው በፈጠራና በቴክኖሎጂ ባላቸው አቅም ነው።
የግብርና፣ የጤና፣ የማዕድን፣ የኢንዱስትሪ እና ሌሎች ልማቶችን በአዳዲስ ፈጠራና ቴክኖሎጂ በማስደገፍ ዕድገትን ለማፋጠን ከታች ጀምሮ መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል።
ለዚህም የሚከናወኑ የፈጠራ ስራዎች ችግር ፈቺና የማሕበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ መሆናቸውን በመፈተሽ ለሁሉም ተደራሽ ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል።
የመማርና ማስተማር ስራውም በፈጠራና ቴክኖሎጂ ማላመድ ላይ ያተኮረ እንዲሆን እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው፤ ለዚህም የመምህራንና የተማሪዎች ድርሻ ከፍ ያለ ነው ብለዋል።
የመምህራንና የተማሪዎች የፈጠራ ስራዎችን በማበረታታት ልማት ላይ እንዲውሉ እየተመቻቸ እንደሆነም ገልጸዋል።
የአማራ ክልል ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ምክትል ኃላፊ የቻለ ይግዛው በበኩላቸው፤ ልማትን ለማፋጠንና የሕብረተሰቡን አኗኗር ለማዘመን አዳዲስ የፈጠራ ስራዎች እንደሚያስፈልጉ ተናግረዋል።
ለዚህም ተማሪዎችና መምህራን በፈጠራ ያገኟቸውን ስራዎች ለልማት እንዲውሉ መደገፍና ማበረታታት እንደሚገባ አመልክተዋል።
በአውደ ርዕዩ የቀረቡ የፈጠራ ስራዎች ወደ ተግባር ተቀይረው ጥቅም ላይ እንዲውሉ ቢሮው አስፈላጊውን ቴክኒካል ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል።
በአውደ ርዕዩ የ11ኛ ክፍል የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪ የሆነችው ሊዲያ ባዬ፤ ከአራት ጓደኞቿ ጋር በመሆን አየርን በማመቅ ውሃን ያለነዳጅ ገፍቶ በማውጣት ለመስኖ ልማት የሚያውል ቴክኖሎጂ መፍጠራቸውን አስታውቃለች።
ቴክኖሎጂው የነዳጅ ዋጋ በየጊዜው በመጨመሩ ምክንያት የሚገጥመውን ችግር በመቋቋም አርሶ አደሮች በቀላል ወጪ የመስኖ ልማትን ማቀላጠፍ የሚያስችል መሆኑን አስረድታለች።
ከግንቦት 22 እስከ 25/2017 ዓ.ም ለሕዝብ ክፍት ሆኖ ለዕይታ በሚቆየው አውደ ርዕይ በተማሪዎችና በመምህራን የተዘጋጁ ከ100 በላየ የተለያዩ የፈጠራ ስራዎች መቅረባቸውም ታውቋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025
ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...
Feb 28, 2025
ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...
Feb 24, 2025