የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በክልሉ የመምህራንና ተማሪዎች የፈጠራ ስራዎችን በማበረታታት ልማት ላይ እንዲውሉ እየተመቻቸ ነው

Jun 3, 2025

IDOPRESS

ባህርዳር፤ ግንቦት 23/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል በመምህራንና ተማሪዎች የሚከናወኑ የፈጠራ ስራዎችን በማበረታታት ልማት ላይ እንዲውሉ እየተመቻቸ መሆኑን የክልሉ ትምህርት ቢሮ ገለጸ።

"ፈጠራ ለሁለንተናዊ ብልፅግና" በሚል መሪ ሃሳብ ትምህርት ቢሮው ያዘጋጀው የተማሪዎችና የመምህራን ክልላዊ የሳይንስ ፈጠራ ስራዎች አውደ ርዕይ ዛሬ ተመርቆ ለዕይታ ቀርቧል።

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮው ኃላፊ ሙሉነሽ ደሴ(ዶ/ር) እንዳሉት፤ የሀገራት ዕድገት የሚለካው በፈጠራና በቴክኖሎጂ ባላቸው አቅም ነው።

የግብርና፣ የጤና፣ የማዕድን፣ የኢንዱስትሪ እና ሌሎች ልማቶችን በአዳዲስ ፈጠራና ቴክኖሎጂ በማስደገፍ ዕድገትን ለማፋጠን ከታች ጀምሮ መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል።

ለዚህም የሚከናወኑ የፈጠራ ስራዎች ችግር ፈቺና የማሕበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ መሆናቸውን በመፈተሽ ለሁሉም ተደራሽ ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል።


የመማርና ማስተማር ስራውም በፈጠራና ቴክኖሎጂ ማላመድ ላይ ያተኮረ እንዲሆን እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው፤ ለዚህም የመምህራንና የተማሪዎች ድርሻ ከፍ ያለ ነው ብለዋል።

የመምህራንና የተማሪዎች የፈጠራ ስራዎችን በማበረታታት ልማት ላይ እንዲውሉ እየተመቻቸ እንደሆነም ገልጸዋል።

የአማራ ክልል ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ምክትል ኃላፊ የቻለ ይግዛው በበኩላቸው፤ ልማትን ለማፋጠንና የሕብረተሰቡን አኗኗር ለማዘመን አዳዲስ የፈጠራ ስራዎች እንደሚያስፈልጉ ተናግረዋል።

ለዚህም ተማሪዎችና መምህራን በፈጠራ ያገኟቸውን ስራዎች ለልማት እንዲውሉ መደገፍና ማበረታታት እንደሚገባ አመልክተዋል።

በአውደ ርዕዩ የቀረቡ የፈጠራ ስራዎች ወደ ተግባር ተቀይረው ጥቅም ላይ እንዲውሉ ቢሮው አስፈላጊውን ቴክኒካል ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል።

በአውደ ርዕዩ የ11ኛ ክፍል የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪ የሆነችው ሊዲያ ባዬ፤ ከአራት ጓደኞቿ ጋር በመሆን አየርን በማመቅ ውሃን ያለነዳጅ ገፍቶ በማውጣት ለመስኖ ልማት የሚያውል ቴክኖሎጂ መፍጠራቸውን አስታውቃለች።

ቴክኖሎጂው የነዳጅ ዋጋ በየጊዜው በመጨመሩ ምክንያት የሚገጥመውን ችግር በመቋቋም አርሶ አደሮች በቀላል ወጪ የመስኖ ልማትን ማቀላጠፍ የሚያስችል መሆኑን አስረድታለች።

ከግንቦት 22 እስከ 25/2017 ዓ.ም ለሕዝብ ክፍት ሆኖ ለዕይታ በሚቆየው አውደ ርዕይ በተማሪዎችና በመምህራን የተዘጋጁ ከ100 በላየ የተለያዩ የፈጠራ ስራዎች መቅረባቸውም ታውቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026