የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የከተማ አስተዳደሩ ባመቻቸው የስራ ዕድል ወጣቶች የኢኮኖሚ ተጠቃሚነታቸው አድጓል

Jun 3, 2025

IDOPRESS

ደብረ ማርቆስ፤ ግንቦት 23/2017(ኢዜአ)፡- የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ያመቻቸላቸው የስራ ዕድል እራሳቸውን በመቻል ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ ምቹ ሁኔታ እንደተፈጠረላቸው በከተማው በጥቃቅንና አነስተኛ የስራ ዘርፎች የተሰማሩ ወጣቶች ተናገሩ።

የአካባቢን ጸጋ በማልማት የስራ አጥነትን ለማቃለል በተደረገው ጥረት እስካሁን ከ17ሺህ 600 በላይ ወጣቶች የስራ ዕድል ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን የከተማ አስተዳደሩ ስራና ስልጠና መምሪያ አስታውቋል።

ይህም ክንውን በበጀት ዓመቱ ከ20ሺህ በላይ ለሚሆኑ ስራ ፈላጊዎች የስራ ዕድል ለመፍጠር ከታቀደው ውስጥ እንደሆነ ተመልክቷል።

ከስራ እድሉ ተጠቃሚዎች መካከል የከተማው ነዋሪ ወጣት የሩቅሰው ታደለ ለኢዜአ በሰጠችው አስተያየት፤ በዚህ በጀት ዓመት ሦስት ሆነው በመደራጀት በዶሮ እርባታ መሰማራታቸውን ገልጻለች።


ወደ ስራው ሲገቡም መንግስት የመስሪያ ቦታ እና 250ሺህ ብር ብድር ማቅረቡን ተናግራለች።

በእስካሁኑም ለሦስት ጊዜ ያህል ጫጩት በማሳደግ ባከናወኑት ግብይት ከ110ሺህ ብር በላይ ገቢ ማግኘታቸውን አስረድታለች።

በዚህም ከስራቸው በሚያገኙት ገቢ ከቤተሰብ ጠባቂነት በመላቀቅ የኢኮኖሚ አቅማቸውን ለማሳደግ ምቹ ሁኔታ እንደተፈጠረላቸው ጠቅሳለች።


ሌላው የከተማው ነዋሪ ወጣት ዳዊት አትንኩት በበኩሉ፤ ከዚህ በፊት ተቀጥሮ ይሰራ እንደነበር አስታውሶ፤ በእንጨትና ብረታ ብረት ዘርፍ ተደራጅተው በመስራታቸው ተጠቃሚ መሆን እንደቻሉ ገልጿል።

አሁን ላይ ከመንግስት ባገኘው 100ሺህ ብር መነሻ ካፒታል በግሉ እየሰራ እንደሚገኝ ተናግሯል።

የከተማ አስተዳደሩ ስራና ስልጠና መምሪያ ሃላፊ መኮነን ሙሉአዳም እንዳሉት፤ የአካባቢን ጸጋ በማልማት ስራ አጥነትን ለማቃለል እየተሰራ ነው።

በዚህም በበጀት ዓመቱ ከ20ሺህ በላይ ለሚሆኑ ስራ ፈላጊዎች የስራ እድል ለመፍጠር ከታቀደው ውስጥ በእስካሁኑ ከ17ሺህ 600 በላይ ለሚሆኑ ወጣቶች የስራ እድል ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን አስታውቀዋል።

በኮንስትራክሽን፣ በአገልግሎት፣ በከተማ ግብርና፣ በማኑፋክቸሪንግ እና በሌሎችም ዘርፎች የስራ እድሉ የተፈጠረ ሲሆን፤ ከ42 ሚሊየን ብር በላይ ብድርና ከ70 በላይ ሼዶች ተመቻችቷል ሲሉ ገልጸዋል።

እቅዱን ለማሳካት በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው፤ የስራ ዕድል ፈጠራውን በማስፋፋት የወጣቶችን ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት መሰጠቱን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የአፍሪካ የልማትና ትብብር ዓርማ - ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በታዋቂው ታይም መጽሔት ገጽ

አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...

Sep 14, 2026

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026