
ድሬደዋ፣ግንቦት 24/2017(ኢዜአ )፦የሎጂስቲክስ ዘርፉን ዘመናዊና ቀልጣፋ ለማድረግ የአሽከርካሪዎች ሚና የላቀ መሆኑን የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ደንጌ ቦሩ ተናገሩ።
የሎጂስቲክስ አገልግሎቱን ለማቀላጠፍ የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች የሚኖራቸውን ሚና ለማሳደግ ያለመ ስልጠና ለአሽከርካሪዎች በድሬደዋ ተሰጥቷል።
የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ ደንጌ ቦሩ በወቅቱ እንደተናገሩት፥ የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች የተጣለባቸውን አገራዊ ተልዕኮ ለመወጣት እያከናወኑ ለሚገኙት ተግባራት ምስጋና ይገባቸዋል።
የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች የሀገርን አደራ ተሸክመው በሚያከናወኑት ስራ ውስጥ ጉልህ ሚና እየተጫወቱ መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህን ጥረታቸውን ከአደጋ በመጠበቅ አጠናክረው እንዲቀጥሉ አስገንዝበዋል።
ተልዕኳቸውን በላቀ ደረጃ ለማሳደግና የሎጂስቲክስ ዘርፉን ቀልጣፋና ፈጣን እንዲሆን የተለያዩ የማሻሻያ አሰራሮች ተዘርግተው በመተግበር ላይ መሆናቸውንም ገልጸዋል።
በተለይም የተጀመረውን የአሰራር ለውጥ በተቀናጀ መንገድ በመተግበር የወጪና ገቢ የንግድ እንቅስቃሴዎችን በላቀ ደረጃ ለማሳደግ የአሽከርካሪዎች ሚና ጉልህ መሆኑን አስገንዝበዋል።
በመሆኑም የሎጀስቲክስ ዘርፍ አካል ለሆነው በትራንስፖርት ዘርፍ ለተሰማሩት የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች እና ባለድርሻዎች በድሬዳዋ የተዘጋጀው ስልጠና ተልዕኮን በፍጥነትና በጥራት ዳር ለማድረስ እንደሚያግዝም አስታውቀዋል።
በድሬደዋ የተዘጋጀው ስልጠና የሎጂስቲክስ ዘርፍን ለማሳደግ መሠረታዊ አስተዋጽኦ ያበረክታል ያሉት ደግሞ የድሬዳዋ አስተዳደር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ወይዘሮ ሽኩሪ አብዱረህማን ናቸው።
በከባድና አስቸጋሪ መልክዓምድር በመጓጓዝ ለሀገርና ለህዝብ ከፍታ እንዲሁም የተጀመረውን አገራዊ የለውጥ ዕውን ለማድረግ እየተጋችሁ ያላችሁ የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ምስጋናና ክብር ይገባችኋሃል ብለዋል።
በስልጠናው ላይ የተሳተፉት የድሬደዋ አስተዳደር ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ዋና አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ በበኩላቸው፥ በድሬደዋ እና በአካባቢው አደጋን በመከላከል እና ጠንቅቆ በማሽከርከር በአብነት የሚጠቀሱት የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች መሆናቸውን አንስተዋል።
ትናንት በተጀመረው ስልጠና ላይ የተሳተፉት የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች እና የዘርፉ ባለድርሻ አካላት በበኩላቸው፥ በሎጂስቲክስ ኢንዱስትሪ የአሽከርካሪዎች ሚና፣ የአሽከርካሪዎች ስነ ባህሪና አደጋ ተከላክሎ የማሽከርከር እንዲሁም በአደጋ ጊዜ ምላሾች ላይ ግንዛቤ ማግኘታቸውን ገልጸዋል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026