የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የሎጂስቲክስ ዘርፉን ፈጣንና ቀልጣፋ ለማድረግ የአሽከርካሪዎች ሚና የላቀ ነው

Jun 3, 2025

IDOPRESS

ድሬደዋ፣ግንቦት 24/2017(ኢዜአ )፦የሎጂስቲክስ ዘርፉን ዘመናዊና ቀልጣፋ ለማድረግ የአሽከርካሪዎች ሚና የላቀ መሆኑን የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ደንጌ ቦሩ ተናገሩ።


የሎጂስቲክስ አገልግሎቱን ለማቀላጠፍ የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች የሚኖራቸውን ሚና ለማሳደግ ያለመ ስልጠና ለአሽከርካሪዎች በድሬደዋ ተሰጥቷል።


የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ ደንጌ ቦሩ በወቅቱ እንደተናገሩት፥ የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች የተጣለባቸውን አገራዊ ተልዕኮ ለመወጣት እያከናወኑ ለሚገኙት ተግባራት ምስጋና ይገባቸዋል።


የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች የሀገርን አደራ ተሸክመው በሚያከናወኑት ስራ ውስጥ ጉልህ ሚና እየተጫወቱ መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህን ጥረታቸውን ከአደጋ በመጠበቅ አጠናክረው እንዲቀጥሉ አስገንዝበዋል።


ተልዕኳቸውን በላቀ ደረጃ ለማሳደግና የሎጂስቲክስ ዘርፉን ቀልጣፋና ፈጣን እንዲሆን የተለያዩ የማሻሻያ አሰራሮች ተዘርግተው በመተግበር ላይ መሆናቸውንም ገልጸዋል።


በተለይም የተጀመረውን የአሰራር ለውጥ በተቀናጀ መንገድ በመተግበር የወጪና ገቢ የንግድ እንቅስቃሴዎችን በላቀ ደረጃ ለማሳደግ የአሽከርካሪዎች ሚና ጉልህ መሆኑን አስገንዝበዋል።


በመሆኑም የሎጀስቲክስ ዘርፍ አካል ለሆነው በትራንስፖርት ዘርፍ ለተሰማሩት የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች እና ባለድርሻዎች በድሬዳዋ የተዘጋጀው ስልጠና ተልዕኮን በፍጥነትና በጥራት ዳር ለማድረስ እንደሚያግዝም አስታውቀዋል።


በድሬደዋ የተዘጋጀው ስልጠና የሎጂስቲክስ ዘርፍን ለማሳደግ መሠረታዊ አስተዋጽኦ ያበረክታል ያሉት ደግሞ የድሬዳዋ አስተዳደር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ወይዘሮ ሽኩሪ አብዱረህማን ናቸው።


በከባድና አስቸጋሪ መልክዓምድር በመጓጓዝ ለሀገርና ለህዝብ ከፍታ እንዲሁም የተጀመረውን አገራዊ የለውጥ ዕውን ለማድረግ እየተጋችሁ ያላችሁ የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ምስጋናና ክብር ይገባችኋሃል ብለዋል።


በስልጠናው ላይ የተሳተፉት የድሬደዋ አስተዳደር ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ዋና አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ በበኩላቸው፥ በድሬደዋ እና በአካባቢው አደጋን በመከላከል እና ጠንቅቆ በማሽከርከር በአብነት የሚጠቀሱት የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች መሆናቸውን አንስተዋል።


ትናንት በተጀመረው ስልጠና ላይ የተሳተፉት የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች እና የዘርፉ ባለድርሻ አካላት በበኩላቸው፥ በሎጂስቲክስ ኢንዱስትሪ የአሽከርካሪዎች ሚና፣ የአሽከርካሪዎች ስነ ባህሪና አደጋ ተከላክሎ የማሽከርከር እንዲሁም በአደጋ ጊዜ ምላሾች ላይ ግንዛቤ ማግኘታቸውን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026