የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የሎጂስቲክስ ዘርፉን ፈጣንና ቀልጣፋ ለማድረግ የአሽከርካሪዎች ሚና የላቀ ነው

Jun 3, 2025

IDOPRESS

ድሬደዋ፣ግንቦት 24/2017(ኢዜአ )፦የሎጂስቲክስ ዘርፉን ዘመናዊና ቀልጣፋ ለማድረግ የአሽከርካሪዎች ሚና የላቀ መሆኑን የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ደንጌ ቦሩ ተናገሩ።


የሎጂስቲክስ አገልግሎቱን ለማቀላጠፍ የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች የሚኖራቸውን ሚና ለማሳደግ ያለመ ስልጠና ለአሽከርካሪዎች በድሬደዋ ተሰጥቷል።


የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ ደንጌ ቦሩ በወቅቱ እንደተናገሩት፥ የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች የተጣለባቸውን አገራዊ ተልዕኮ ለመወጣት እያከናወኑ ለሚገኙት ተግባራት ምስጋና ይገባቸዋል።


የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች የሀገርን አደራ ተሸክመው በሚያከናወኑት ስራ ውስጥ ጉልህ ሚና እየተጫወቱ መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህን ጥረታቸውን ከአደጋ በመጠበቅ አጠናክረው እንዲቀጥሉ አስገንዝበዋል።


ተልዕኳቸውን በላቀ ደረጃ ለማሳደግና የሎጂስቲክስ ዘርፉን ቀልጣፋና ፈጣን እንዲሆን የተለያዩ የማሻሻያ አሰራሮች ተዘርግተው በመተግበር ላይ መሆናቸውንም ገልጸዋል።


በተለይም የተጀመረውን የአሰራር ለውጥ በተቀናጀ መንገድ በመተግበር የወጪና ገቢ የንግድ እንቅስቃሴዎችን በላቀ ደረጃ ለማሳደግ የአሽከርካሪዎች ሚና ጉልህ መሆኑን አስገንዝበዋል።


በመሆኑም የሎጀስቲክስ ዘርፍ አካል ለሆነው በትራንስፖርት ዘርፍ ለተሰማሩት የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች እና ባለድርሻዎች በድሬዳዋ የተዘጋጀው ስልጠና ተልዕኮን በፍጥነትና በጥራት ዳር ለማድረስ እንደሚያግዝም አስታውቀዋል።


በድሬደዋ የተዘጋጀው ስልጠና የሎጂስቲክስ ዘርፍን ለማሳደግ መሠረታዊ አስተዋጽኦ ያበረክታል ያሉት ደግሞ የድሬዳዋ አስተዳደር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ወይዘሮ ሽኩሪ አብዱረህማን ናቸው።


በከባድና አስቸጋሪ መልክዓምድር በመጓጓዝ ለሀገርና ለህዝብ ከፍታ እንዲሁም የተጀመረውን አገራዊ የለውጥ ዕውን ለማድረግ እየተጋችሁ ያላችሁ የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ምስጋናና ክብር ይገባችኋሃል ብለዋል።


በስልጠናው ላይ የተሳተፉት የድሬደዋ አስተዳደር ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ዋና አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ በበኩላቸው፥ በድሬደዋ እና በአካባቢው አደጋን በመከላከል እና ጠንቅቆ በማሽከርከር በአብነት የሚጠቀሱት የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች መሆናቸውን አንስተዋል።


ትናንት በተጀመረው ስልጠና ላይ የተሳተፉት የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች እና የዘርፉ ባለድርሻ አካላት በበኩላቸው፥ በሎጂስቲክስ ኢንዱስትሪ የአሽከርካሪዎች ሚና፣ የአሽከርካሪዎች ስነ ባህሪና አደጋ ተከላክሎ የማሽከርከር እንዲሁም በአደጋ ጊዜ ምላሾች ላይ ግንዛቤ ማግኘታቸውን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የአፍሪካ የልማትና ትብብር ዓርማ - ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በታዋቂው ታይም መጽሔት ገጽ

አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...

Sep 14, 2026

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026