
ድሬደዋ፣ግንቦት 24/2017(ኢዜአ )፦የሎጂስቲክስ ዘርፉን ዘመናዊና ቀልጣፋ ለማድረግ የአሽከርካሪዎች ሚና የላቀ መሆኑን የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ደንጌ ቦሩ ተናገሩ።
የሎጂስቲክስ አገልግሎቱን ለማቀላጠፍ የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች የሚኖራቸውን ሚና ለማሳደግ ያለመ ስልጠና ለአሽከርካሪዎች በድሬደዋ ተሰጥቷል።
የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ ደንጌ ቦሩ በወቅቱ እንደተናገሩት፥ የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች የተጣለባቸውን አገራዊ ተልዕኮ ለመወጣት እያከናወኑ ለሚገኙት ተግባራት ምስጋና ይገባቸዋል።
የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች የሀገርን አደራ ተሸክመው በሚያከናወኑት ስራ ውስጥ ጉልህ ሚና እየተጫወቱ መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህን ጥረታቸውን ከአደጋ በመጠበቅ አጠናክረው እንዲቀጥሉ አስገንዝበዋል።
ተልዕኳቸውን በላቀ ደረጃ ለማሳደግና የሎጂስቲክስ ዘርፉን ቀልጣፋና ፈጣን እንዲሆን የተለያዩ የማሻሻያ አሰራሮች ተዘርግተው በመተግበር ላይ መሆናቸውንም ገልጸዋል።
በተለይም የተጀመረውን የአሰራር ለውጥ በተቀናጀ መንገድ በመተግበር የወጪና ገቢ የንግድ እንቅስቃሴዎችን በላቀ ደረጃ ለማሳደግ የአሽከርካሪዎች ሚና ጉልህ መሆኑን አስገንዝበዋል።
በመሆኑም የሎጀስቲክስ ዘርፍ አካል ለሆነው በትራንስፖርት ዘርፍ ለተሰማሩት የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች እና ባለድርሻዎች በድሬዳዋ የተዘጋጀው ስልጠና ተልዕኮን በፍጥነትና በጥራት ዳር ለማድረስ እንደሚያግዝም አስታውቀዋል።
በድሬደዋ የተዘጋጀው ስልጠና የሎጂስቲክስ ዘርፍን ለማሳደግ መሠረታዊ አስተዋጽኦ ያበረክታል ያሉት ደግሞ የድሬዳዋ አስተዳደር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ወይዘሮ ሽኩሪ አብዱረህማን ናቸው።
በከባድና አስቸጋሪ መልክዓምድር በመጓጓዝ ለሀገርና ለህዝብ ከፍታ እንዲሁም የተጀመረውን አገራዊ የለውጥ ዕውን ለማድረግ እየተጋችሁ ያላችሁ የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ምስጋናና ክብር ይገባችኋሃል ብለዋል።
በስልጠናው ላይ የተሳተፉት የድሬደዋ አስተዳደር ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ዋና አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ በበኩላቸው፥ በድሬደዋ እና በአካባቢው አደጋን በመከላከል እና ጠንቅቆ በማሽከርከር በአብነት የሚጠቀሱት የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች መሆናቸውን አንስተዋል።
ትናንት በተጀመረው ስልጠና ላይ የተሳተፉት የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች እና የዘርፉ ባለድርሻ አካላት በበኩላቸው፥ በሎጂስቲክስ ኢንዱስትሪ የአሽከርካሪዎች ሚና፣ የአሽከርካሪዎች ስነ ባህሪና አደጋ ተከላክሎ የማሽከርከር እንዲሁም በአደጋ ጊዜ ምላሾች ላይ ግንዛቤ ማግኘታቸውን ገልጸዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026