የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በሀገር ውስጥ የሥራ ስምሪት ከ3 ነጥብ 4 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ቋሚ የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ሆነዋል

Jun 5, 2025

IDOPRESS

ሆሳዕና፤ግንቦት 27/2017 (ኢዜአ)፦በበጀት ዓመቱ አሥር ወራት በሀገር ውስጥ የሥራ ስምሪት ከ3 ነጥብ 4 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ቋሚ የሥራ ዕድል ተጠቃሚ መሆናቸውን የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ገለጸ።

ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት በሚኒስቴሩ የሥራ ስምሪትና ገበያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሰለሞን ሶካ እንደገለጹት፣በበጀት ዓመቱ ዜጎችን በተለያዩ የሥራ ዘርፎች ተጠቃሚ ለማድረግ ሲሰራ ቆይቷል።

ባለፉት አስር ወራትም በሀገር ውስጥ የሥራ ስምሪት 4 ነጥብ 2 ሚሊዮን ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ ታቅዶ ከ3 ነጥብ 4 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን ቋሚ የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል ብለዋል።

የሥራ ዕድሉ በግብርና፣በኢንዱስትሪና በአገልግሎት ዘርፍ የተፈጠረ መሆኑንም ጠቅሰዋል።

ለክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራ ትኩረት መሰጠቱን ጠቁመው፣ በተከናወነው የሪፎርም ሥራም ተስፋ ሰጪ ውጤት እየተመዘገበ መምጣቱን ገልጸዋል፡፡

ኢኮኖሚው የሚፈለገውን የሰው ኃይል ለማፍራት በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ተቋማት የየአካባቢያቸውን ጸጋ መሰረት ያደረጉ አጫጭር ስልጠናዎች እየተሰጡ ይገኛል ሲሉም ተናግረዋል፡፡

በስልጠናው ዜጎች በቂ እውቀትና ሙያ አግኝተው እንዲወጡ ከማድረግ ባለፈ በሰለጠኑበት ዘርፍ የሥራ እድል እንዲያገኙም ምቹ ሁኔታ እየተፈጠረ መሆኑንም ጠቅስዋል፡፡

የሚፈጠረው የሥራ ዕድል ከሀገሪቱ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ጋር የተሳሰረ መሆን እንዳለበት የገለጹት ሚኒስትር ዴኤታው፥በአምስቱ የኢኮኖሚ አውታሮች ለዜጎች የሥራ ዕድል በመፍጠር ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑንም አክለዋል፡፡

ለዚህም ስኬት የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ተቋማት የአካባቢያቸውን ፀጋ ማዕከል ያደረገ ክህሎት መር ስልጠና እንዲሰጡ እየተደረገ መሆኑንም ተናግረዋል።


የሀዲያ ዞን የሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ፋንታሁን ሊራንሶ በበኩላቸው፥ በዞኑ ባለፉት 10 ወራት ለ88 ሺህ ወጣቶች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ ዕድል ተፈጥሯል።

ከተለያዩ ተቋማት ጋር በመቀናጀት በየአካባቢው ያለውን ፀጋ መሰረት ያደረገ ክህሎት መር ስልጠና እንዲያገኙ እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰው፣ ወጣቶች በከተማና በገጠር ግብርና፣በኢንዱስትሪና በአገልግሎት ዘርፍ እንዲሰማሩ መደረጉን ተናግረዋል።

በሆሳዕና ከተማ የውሃ ልማት ቴራዞና ብሎኬት ማምረቻ ኢንተርፕራይዝ ሰብሳቢ ወጣት በለጠ ደገፈ እንደገለፀው፣ በበጀት ዓመቱ በ10 ሰዎች በመደራጀት ከመንግስት በብድር ባገኙት 1 ሚሊዮን 200 ሺህ ብር ካፒታል ሥራ ጀምረዋል፡፡


በዚህም ከራሳቸው ባለፈ ለ45 ወጣቶች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ እድል መፍጠራቸውን ጠቁሞ፣ ሰርተው በሚያገኙት ገቢ ከመንግስት የወሰዱትን ብድር ከመመለስ ባለፈ ቁጠባ መጀመራቸውን ተናግረዋል፡፡

በኢንተርፕራይዙ የሥራ ዕድል የተፈጠረላት የኮምፒዩተር ሳይንስ ተመራቂዋ ወጣት ገነት ወንድሙ በበኩሏ፥መንግስት ወጣቶች ወደስራ እንዲገቡ የተለያዩ ማበረታቻዎችን እያደረገ መሆኑን ጠቅሳ፣ በተፈጠረላት የሥራ ዕድል ተጠቃሚ መሆኗን ተናግራለች።


የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025