
ድሬደዋ፣ ግንቦት 27/2017(ኢዜአ)፡-የኮሪደር ልማቱ የከተማውን ውበትና ገፅታ እያጎላና ፤የስራና የማህበራዊ አገልግሎት ችግሮችን እየፈታ መሆኑን አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የድሬደዋ ነዋሪዎች ተናገሩ።
በድሬደዋ በመጀመሪያው ምዕራፍ እየተገነባ የሚገኘው 12 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት የማጠናቀቂያ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑም ተመላክቷል።
አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡት የድሬደዋ ነዋሪዎች እንደተናገሩት፤ ደረጃውን ጠብቆ በተለያዩ የከተማው አቅጣጫዎች የተገነባው የኮሪደር ልማት ድሬዳዋን ውብና ማራኪ የስራና የመኖሪያ ማዕከል አድርጓታል።
ከከተማው ነዋሪዎች መካከል አቶ ፍቃዱ አበበ እንደገለፁት፤ የኮሪደር ልማቱ ተጨማሪ የተሽከርካሪዎችና የብስክሌት መንገዶች የፈጠረና ማህበራዊ ችግሮችን ያቃለለ ትልቅ ልማት ነው።

አቶ ታደለ ወልዴ በበኩላቸው የኮሪደር ልማቱ ከራሳቸው ጀምሮ ለብዙ ነዋሪዎች የስራ እድል ከመፍጠር በዘለለ የከተማውን ገፅታ በላቀ ደረጃ እየለወጠው ነው ብለዋል።
በልማቱ በፍጥነትና በጥራት ወደ ልዩ ውበት የቀየረና የነዋሪዎች መዝናኛ ስፍራ እየሆነ መምጣቱን የገለፁት ደግሞ ወይዘሮ ዘበናይ ተሰማ ናቸው።

በተለይም የነገ አገር ተረካቢ ህፃናት ከየአቅጣጫው ተሰባሰበው በአንድነት የሚዝናኑበት ስፍራ መሆኑ የልጆችን ፍቅር እና አንድነት የሚያጠናክር ይሆናል ብለዋል።
ከባሌ ሮቤ እንደመጣ የተናገረው ወጣት አብደላ ዑመር የኮሪደር ልማቱ ድሬዳዋን ይበልጥ ውብና ማራኪ ከተማ እንዳደረጋት ገልፅዋል።

አስተያየት ሰጪዎቹ አክለው የተሰሩትን ልማቶች በተናጠልና በተቀናጀ መንገድ በመንከባከብ ዘላቂ ጥቅም እንዲሰጡ ከማድረግ በተጨማሪ በምዕራፍ ሁለት የኮሪደር ልማት ላይ አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ መዘጋጀታቸውን አስረድተዋል ።
በከተማው አምስት አቅጣጫዎች የተጀመረው 12 ኪሎ ሜትር የመጀመሪያው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት የተሽከርካሪ ፣ የብስክሌት ፣ የእግረኛ መንገዶችን በውስጡ ያካተተ ሲሆን አሁን ላይ ልማቱ በመጠናቀቅ ላይ መሆኑም ታውቋል።
አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...
Sep 14, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026