
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 27/2017(ኢዜአ)፦ የጎንደር ከተማ ወደ ሠላም መመለሷ በርካታ ልማቶች በስኬት እንዲከናወኑ ማስቻሉን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ተናገሩ።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በጎንደር ከተማ የተለያዩ የልማት ሥራዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።
በጉብኝታቸውም ከአኩሪ አተር የምግብ ዘይት የሚያመርት ፋብሪካን መርቀው ሥራ ያስጀመሩ ሲሆን፤ በክልል ደረጃ በጎንደር ከተማ የተዘጋጀውን የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ የቀረቡ ምርቶችንም ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
በጎንደር ከተማ የኮሪደር ልማት እንዲሁም የአጼ ፋሲል ቤተ-መንግሥት እድሳትንም ጎብኝተዋል።

ጉብኝቱን አስመልክቶ ማብራሪያ የሰጡት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ ጎንደር ከተማ ተከስቶ ከነበረው የጸጥታ ችግር በመውጣት ትልልቅ የልማት ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑን ተመልክተናል ብለዋል።
በኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖም በምግብ ማቀነባበር መስክ የተሰማሩ፣ በጨርቃጨርቅ ኢንዱስትሪ ከሀገር አልፎ ለውጭ ገበያ መቅረብ የሚችሉ ምርቶችን መመልከታቸውን ገልጸው፤ በዚህም ትልቅ አቅም እየተፈጠረ መሆኑን ተገንዝበናል ነው ያሉት።
በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብርም ውጤታማ እንቅስቃሴ መኖሩን የሚያመላክቱ ስኬቶችን አይተናል ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህም ሠላም በመስፈኑ የተገኘ ውጤት ነው ብለዋል።

በኮሪደር ልማትም በጎንደር ከተማ ኀብረተሰቡን በማሳተፍ የተከናወኑ ተግባራት በአርአያነት የሚወሰዱ መሆናቸውን አንስተዋል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በከተማዋ የኮሪደር ልማቱ በጥሩ የአፈጻጸም ደረጃ ላይ መሆኑንም እንዲሁ።

የፋሲል ቤተ-መንግሥት እድሳት ለጎንደር ከተማ ኮሪደር ልማት ትልቅ መነቃቃት መፍጠሩንም አብራርተዋል።
የቤተ መንግሥቱ እድሳት የቅርሱን ይዘት እንደጠበቀ በመከናወን ላይ እንደሚገኝ ጠቅሰው ይህም ለሌሎች ግንባታዎች ምሳሌ የሚሆን ውጤት የተገኘበት ነው ብለዋል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026