
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 27/2017(ኢዜአ)፦ የጎንደር ከተማ ወደ ሠላም መመለሷ በርካታ ልማቶች በስኬት እንዲከናወኑ ማስቻሉን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ተናገሩ።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በጎንደር ከተማ የተለያዩ የልማት ሥራዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።
በጉብኝታቸውም ከአኩሪ አተር የምግብ ዘይት የሚያመርት ፋብሪካን መርቀው ሥራ ያስጀመሩ ሲሆን፤ በክልል ደረጃ በጎንደር ከተማ የተዘጋጀውን የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ የቀረቡ ምርቶችንም ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
በጎንደር ከተማ የኮሪደር ልማት እንዲሁም የአጼ ፋሲል ቤተ-መንግሥት እድሳትንም ጎብኝተዋል።

ጉብኝቱን አስመልክቶ ማብራሪያ የሰጡት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ ጎንደር ከተማ ተከስቶ ከነበረው የጸጥታ ችግር በመውጣት ትልልቅ የልማት ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑን ተመልክተናል ብለዋል።
በኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖም በምግብ ማቀነባበር መስክ የተሰማሩ፣ በጨርቃጨርቅ ኢንዱስትሪ ከሀገር አልፎ ለውጭ ገበያ መቅረብ የሚችሉ ምርቶችን መመልከታቸውን ገልጸው፤ በዚህም ትልቅ አቅም እየተፈጠረ መሆኑን ተገንዝበናል ነው ያሉት።
በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብርም ውጤታማ እንቅስቃሴ መኖሩን የሚያመላክቱ ስኬቶችን አይተናል ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህም ሠላም በመስፈኑ የተገኘ ውጤት ነው ብለዋል።

በኮሪደር ልማትም በጎንደር ከተማ ኀብረተሰቡን በማሳተፍ የተከናወኑ ተግባራት በአርአያነት የሚወሰዱ መሆናቸውን አንስተዋል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በከተማዋ የኮሪደር ልማቱ በጥሩ የአፈጻጸም ደረጃ ላይ መሆኑንም እንዲሁ።

የፋሲል ቤተ-መንግሥት እድሳት ለጎንደር ከተማ ኮሪደር ልማት ትልቅ መነቃቃት መፍጠሩንም አብራርተዋል።
የቤተ መንግሥቱ እድሳት የቅርሱን ይዘት እንደጠበቀ በመከናወን ላይ እንደሚገኝ ጠቅሰው ይህም ለሌሎች ግንባታዎች ምሳሌ የሚሆን ውጤት የተገኘበት ነው ብለዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026