
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 27/2017(ኢዜአ)፦ የጎንደር ከተማ ወደ ሠላም መመለሷ በርካታ ልማቶች በስኬት እንዲከናወኑ ማስቻሉን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ተናገሩ።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በጎንደር ከተማ የተለያዩ የልማት ሥራዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።
በጉብኝታቸውም ከአኩሪ አተር የምግብ ዘይት የሚያመርት ፋብሪካን መርቀው ሥራ ያስጀመሩ ሲሆን፤ በክልል ደረጃ በጎንደር ከተማ የተዘጋጀውን የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ የቀረቡ ምርቶችንም ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
በጎንደር ከተማ የኮሪደር ልማት እንዲሁም የአጼ ፋሲል ቤተ-መንግሥት እድሳትንም ጎብኝተዋል።

ጉብኝቱን አስመልክቶ ማብራሪያ የሰጡት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ ጎንደር ከተማ ተከስቶ ከነበረው የጸጥታ ችግር በመውጣት ትልልቅ የልማት ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑን ተመልክተናል ብለዋል።
በኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖም በምግብ ማቀነባበር መስክ የተሰማሩ፣ በጨርቃጨርቅ ኢንዱስትሪ ከሀገር አልፎ ለውጭ ገበያ መቅረብ የሚችሉ ምርቶችን መመልከታቸውን ገልጸው፤ በዚህም ትልቅ አቅም እየተፈጠረ መሆኑን ተገንዝበናል ነው ያሉት።
በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብርም ውጤታማ እንቅስቃሴ መኖሩን የሚያመላክቱ ስኬቶችን አይተናል ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህም ሠላም በመስፈኑ የተገኘ ውጤት ነው ብለዋል።

በኮሪደር ልማትም በጎንደር ከተማ ኀብረተሰቡን በማሳተፍ የተከናወኑ ተግባራት በአርአያነት የሚወሰዱ መሆናቸውን አንስተዋል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በከተማዋ የኮሪደር ልማቱ በጥሩ የአፈጻጸም ደረጃ ላይ መሆኑንም እንዲሁ።

የፋሲል ቤተ-መንግሥት እድሳት ለጎንደር ከተማ ኮሪደር ልማት ትልቅ መነቃቃት መፍጠሩንም አብራርተዋል።
የቤተ መንግሥቱ እድሳት የቅርሱን ይዘት እንደጠበቀ በመከናወን ላይ እንደሚገኝ ጠቅሰው ይህም ለሌሎች ግንባታዎች ምሳሌ የሚሆን ውጤት የተገኘበት ነው ብለዋል።
አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...
Sep 14, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026