
አዲስ አበባ፤ግንቦት 28/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያና ኬኒያ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ውህደትን የሚያሳልጡ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶችን በመገንባት ለአህጉራዊ ርዕይ ስኬት በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ አስታወቁ።
በምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣልን (ኢጋድ) አስተባባሪነት በኢትዮጵያ እና ኬንያ መካከል በአፍሪካ ቀንድ የሁለትዮሽ ትብብር ልማት ፕሮጀክቶች ላይ በአዲስ አበባ የውይይት መድረክ ተካሂዷል።
በመድረኩ የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ ዴንጌ ቦሩ፤ የኬኒያ ብሔራዊ ግምጃ ቤት የኢንቨስትመንትና የንብረት አስተዳደር ሲሪል ኦዴዴ፣ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
የምክክር መድረኩ ዋና ዓላማም የኢትዮ-ኬንያን የመሠረተ ልማት ትስስርን በማሳደግ በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማት፣በንግድና ድንበር ተሻጋሪ ልማት ትብብርን ለማሳደግ ያለመ ነው።
የኬንያ የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ባለስልጣን የፕሮግራሞች እና ደረጃዎች ዳይሬክተር ቶማስ ብዋሊ በውይይቱ ወቅት፥አገራቱ የተስማሙባቸውን ጉዳዮች አስመልክተው መግለጫ ሰጥተዋል።
በዚህም ውይይቱ ድንበር ተሻጋሪ ትብብር፣ የንግድ ማመቻቸት እና ተግዳሮቶችን በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለመፍታት የጋራ ቁርጠኝነትን በድጋሚ አረጋግጠዋል ብለዋል።
የድንበር ተሻጋሪ የውሃ ሃብቶችን ለማህበረሰቡ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት ለማዋል የሀብት ማሰባሰብ እቅድን ለማደስ መስማማታቸውን ጠቁመዋል።
ለቀጣናዊ ውህደት የጋራ ቁርጠኝነት እና ቀጣይነት ያለው ሰላም፣ ትስስር እና ሁሉን አቀፍ ልማትን ለማስቀጠል በጋራ ኃላፊነት እንደሚሰሩ ማረጋገጣቸውን ተናግረዋል።
የአፍሪካ ቀንድ ልማት ኢኒሼቲቭ በኢትዮጵያ-ኬንያ ድንበር ላይ የሸቀጦችን፣ የሰዎችን እና የዲጂታል አገልግሎቶችን እንቅስቃሴ ለማሻሻል የለውጥ ፕሮግራም መሆኑ መመላከቱን ጠቁመዋል።
እንዲሁም የድንበር ተሻጋሪ የውሃ ሃብቶችን ለህብረተሰባችን የጋራ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት ለማዋል የግብዓት ማሰባሰብያ እቅድን ማነቃቃት የሚያስችል ምክክር በድጋሚ እንዲቀጥል ስብሰባው ከስምምነት ተደርሷል ብለዋል።
የአፍሪካ ቀንድ ልማት ተነሳሽነት በኢትዮጵያ እና በኬንያ ድንበር ላይ የሸቀጦችን፣ የሰዎችንና የዲጂታል አገልግሎቶችን እንቅስቃሴ የማሻሻል መርሃ ግብሮች እንዲካሄዱ ውሳኔ መተላለፉን ተናግረዋል።
አገራቱ ድንበር ተሻጋሪ የፋይበር ኦፕቲክ ግንኙነትን ለማጠናቀቅ፣ ድንበር ዘለል ዲጂታል አገልግሎቶችን ለማሻሻል፣የዲጂታል ስራዎችን ተደራሽነት እና አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን ለማሻሻል ቁርጠኛ መሆናቸውን በውይይቱ ማረጋገጣቸውን አመላክተዋል።
አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...
Sep 14, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026