የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ኢትዮጵያና ኬንያ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶችን በመገንባት ለአህጉራዊ ርዕይ ስኬት በቁርጠኝነት ይሰራሉ

Jun 6, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ግንቦት 28/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያና ኬኒያ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ውህደትን የሚያሳልጡ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶችን በመገንባት ለአህጉራዊ ርዕይ ስኬት በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ አስታወቁ።


በምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣልን (ኢጋድ) አስተባባሪነት በኢትዮጵያ እና ኬንያ መካከል በአፍሪካ ቀንድ የሁለትዮሽ ትብብር ልማት ፕሮጀክቶች ላይ በአዲስ አበባ የውይይት መድረክ ተካሂዷል።


በመድረኩ የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ ዴንጌ ቦሩ፤ የኬኒያ ብሔራዊ ግምጃ ቤት የኢንቨስትመንትና የንብረት አስተዳደር ሲሪል ኦዴዴ፣ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።


የምክክር መድረኩ ዋና ዓላማም የኢትዮ-ኬንያን የመሠረተ ልማት ትስስርን በማሳደግ በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማት፣በንግድና ድንበር ተሻጋሪ ልማት ትብብርን ለማሳደግ ያለመ ነው።


የኬንያ የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ባለስልጣን የፕሮግራሞች እና ደረጃዎች ዳይሬክተር ቶማስ ብዋሊ በውይይቱ ወቅት፥አገራቱ የተስማሙባቸውን ጉዳዮች አስመልክተው መግለጫ ሰጥተዋል።


በዚህም ውይይቱ ድንበር ተሻጋሪ ትብብር፣ የንግድ ማመቻቸት እና ተግዳሮቶችን በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለመፍታት የጋራ ቁርጠኝነትን በድጋሚ አረጋግጠዋል ብለዋል።


የድንበር ተሻጋሪ የውሃ ሃብቶችን ለማህበረሰቡ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት ለማዋል የሀብት ማሰባሰብ እቅድን ለማደስ መስማማታቸውን ጠቁመዋል።


ለቀጣናዊ ውህደት የጋራ ቁርጠኝነት እና ቀጣይነት ያለው ሰላም፣ ትስስር እና ሁሉን አቀፍ ልማትን ለማስቀጠል በጋራ ኃላፊነት እንደሚሰሩ ማረጋገጣቸውን ተናግረዋል።


የአፍሪካ ቀንድ ልማት ኢኒሼቲቭ በኢትዮጵያ-ኬንያ ድንበር ላይ የሸቀጦችን፣ የሰዎችን እና የዲጂታል አገልግሎቶችን እንቅስቃሴ ለማሻሻል የለውጥ ፕሮግራም መሆኑ መመላከቱን ጠቁመዋል።


እንዲሁም የድንበር ተሻጋሪ የውሃ ሃብቶችን ለህብረተሰባችን የጋራ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት ለማዋል የግብዓት ማሰባሰብያ እቅድን ማነቃቃት የሚያስችል ምክክር በድጋሚ እንዲቀጥል ስብሰባው ከስምምነት ተደርሷል ብለዋል።


የአፍሪካ ቀንድ ልማት ተነሳሽነት በኢትዮጵያ እና በኬንያ ድንበር ላይ የሸቀጦችን፣ የሰዎችንና የዲጂታል አገልግሎቶችን እንቅስቃሴ የማሻሻል መርሃ ግብሮች እንዲካሄዱ ውሳኔ መተላለፉን ተናግረዋል።


አገራቱ ድንበር ተሻጋሪ የፋይበር ኦፕቲክ ግንኙነትን ለማጠናቀቅ፣ ድንበር ዘለል ዲጂታል አገልግሎቶችን ለማሻሻል፣የዲጂታል ስራዎችን ተደራሽነት እና አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን ለማሻሻል ቁርጠኛ መሆናቸውን በውይይቱ ማረጋገጣቸውን አመላክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026