
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 29/2017(ኢዜአ)፦ ያልተደመረ አቅም ሀብትና እውቀት የምናስበውን ብልጽግና አያረጋግጥም ሲሉ ጠቅለይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከኢትዮጵያ ቴሌቭዥን ጋር ባደረጉት ልዩ ቆይታ በኢትዮጵያ ቆላማ አካባቢ የተወሰደውን የእይታ ለውጥ በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በማብራሪያቸውም አንዱ የዕይታ ለውጥ የመጣው የኢትዮጵያን ሰው፣ መሬት እና ዕውቀት ከጫፍ ጫፍ መጠቀም አለብን መደመር አለብን የሚለው እንደሚገኝበት ገልጸዋል።
በዚህም የኢትዮጵያ ቆላማ አካባቢ ያለውን የሰው፣ የመሬት እና የውሃ ሀብት ለልማት ግብዓት እንዲሆን ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑንና ይህም የመደመር ዋነኛው እሳቤ መሆኑን ተናግረዋል።
የቆላ ልማት ሀገሪቱን የማወቅ ሀብታችንን የማወቅ አቅማችንን የማወቅ እና የመጠቀም ፍላጎታችን አካል ነው ሲሉም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል።
የሀገሪቱን ሀብት በወጉ ሳናውቅ አቅማችንን ሳናውቅ ያንን አሰናስለን መደመር ሳንችል የምናስበውን ብልጽግና ማረጋገጥ አንችልም ነው ያሉት።
ደቡብ ኦሞን በማሳያነት የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ያለውን የውሃ እና የመሬት ሀብት ከግምት በማስገባት 145 ኪሎ ሜትር ትልልቅ ካናል መሰራቱን ገልጸዋል።
ይህን ማሽን በመጠቀም ማልማት ከተቻለ በምግብ ራስን ለመቻል እና የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በምናደርገው ጥረት ውስጥ የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ ነው ብለዋል።
በተመሳሳይም በሶማሌ፣ በአፋር እና በኦሮሚያ ክልል ቦረና አካባቢ ተመሳሳይ ሀብት ያለባቸው መሆናቸውን ጠቁመው ቆላ አካባቢ ሰፊ የመሬት ሀብት የሚገኝበት መሆኑንም ጨምረው ገልጸዋል።
ቆላ አካባቢዎች በተፈጥሯዊ የመሬት አቀማመጣቸው ምክንያት የመሬት እና የውሃ ሀብት ያለበት በማሽን ለመጠቀም አስቻይ ሁኔታ ያለበት መሆኑንም ጠቁመዋል።
በመሆኑም እነዚህን አካባቢዎች ሳናለማ የምግብ ሉዓላዊነትም ሆነ ብልጽግና በተሟላ መንገድ ሊመጣ አይችልም ነው ያሉት።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026