የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በክልሉ በመኸር ወቅት ለማልማት ከታቀደው ከ88 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በሰብል ተሸፍኗል

Jun 9, 2025

IDOPRESS

ጋምቤላ፣ግንቦት 30/2017 (ኢዜአ)፦በጋምቤላ ክልል በመኸር ወቅት ለማልማት ከታቀደው ከ88 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ቀድመው በሚዘሩ የሰብል ዓይነቶች መሸፈኑን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ቢሮ አስታወቀ።


በክልሉ በመኸር ወቅት ግብርና የምርት ማሳደጊያ ግብዓቶችንና የኩታ-ገጠም እርሻን በመጠቀም ምርታማነትን ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም ቢሮው ገልጿል።


የቢሮው ኃላፊ አቶ ፓል ቱት ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በክልሉ የግብርናውን ልማት በማጠናከርና በማዘመን ምርታማነትን በማሳደግ እንደ ሀገር የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የታለመውን ግብ ለማሳካት በትኩረት እየተሰራ ነው።


በክልሉ በዘንድሮው የመኸር እርሻ ከ172 ሺህ 230 ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ የሰብልና የጓሮ አትክልቶች በማልማት ከ5 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ ነው ብለዋል።


በእስካሁኑ የመኸር እርሻ እንቅስቃሴም ለማልማት ከታቀደው መሬት ከ88 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆነው ቀድመው በሚዘሩ የበቆሎ፣የሰሊጥ፣ የለውዝና ሌሎች የሰብል ዓይነቶች መሸፈኑን ገልጸዋል።


በተለይም በዘንድሮው ዓመት አርሶና አርብቶ አደሩን እንዲሁም ከባለሃብቱ ጋር በማቀናጀት የአፈር ማዳበሪያ ግብዓትን ተጠቅመው ምርታማነታቸውን እንዲያሳድጉ የድጋፍና ክትትል ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል።


በተጨማሪም የአርሶና አርብቶ አደሩን አደረጃጀት በማጠናከር የኩታ ገጠም እርሻ ስራዎችን በማስፋት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ እንደሚገኝም ኃላፊው ተናግረዋል።


በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት የታቀደው መሬት ከቀዳሚው ዓመት ጋር ሲነፃፀርም በ6 ሺህ፣ለመሰብሰብ ከታቀደው ምርት መጠን ደግሞ በ600 ሺህ ኩንታል ብልጫ እንዳለውም ተመላክቷል።


በአበቦ ወረዳ የዋንካክ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ኡጆዎ ኡጁሉ በሰጡት አስተያየት፥ የዘንድሮው የመኸር እርሻ አጋጥሞ ከነበረው መጠነኛ የዝናብ መቆራረጥ በስተቀር በጥሩ ሂደት ላይ መሆኑን ተናግረዋል።


ለዘንደሮው የመኸር እርሻ አስፈላጊውን ዝግጅት በማድረግ ወደ ስራ በመግባት ቀድመው የሚዘሩ ሰብሎችን መዝራታቸውን የገለጹት ደግሞ ሌላው የዚሁ ወረዳ የመንደር ዘጠኝ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር አዲሱ ብሩቃ ናቸው።


በቀጣይ ጊዜም የሩዝ ፣የማሽላ፣የማሾና ሌሎች ሰብል ዓይነቶች የሚዘራበት በመሆኑ ቀሪ ማሳቸውን በተጠቀሱት የሰብል ዓይነቶች ለመሸፈን እየሰሩ መሆናቸውን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የአፍሪካ የልማትና ትብብር ዓርማ - ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በታዋቂው ታይም መጽሔት ገጽ

አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...

Sep 14, 2026

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026