
ወራቤ፤ ሰኔ 2/2017(ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ተግባራዊ የሚደረጉ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች የአካባቢን ብክለት መከላከልን ማዕከል እንዲያደርጉ በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ደንና አካባቢ ጥበቃ ልማት ቢሮ ገለፀ፡፡
ቢሮው ከክልሉ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ልማት ቢሮ ጋር በመተባበር በክልሉ የሚገኙ ፋብሪካዎችና የልማት ፕሮጀክቶች የአካባቢ ብክለት ተፅዕኖን ለመከላከል ያለመ የምክክር መድረክ በወራቤ ከተማ አካሂዷል፡፡

የቢሮው ኃላፊ አብርሃም መጫ በወቅቱ እንዳሉት ቢሮው የተፈጥሮ ሀብትን በመንከባከብ ፅዱ አካባቢን ለመፍጠር በርካታ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል፡፡
በዚህም የክልሉ ከተሞችን ፅዱና የአካባቢ ብክለትን ታሳቢ ያደረጉ ተግባራትን በማከናወን የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም የሚችሉ ሀገር በቀል ችግኞችን እየተከሉ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
በተጨማሪም በክልሉ በኢንቨስትመንት ዘርፍ የተሰማሩ አካላት የአካባቢን ብክለት መከላከልን መሰረት ያደረጉ እንዲሆኑ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ እንደሚገኝም አክለዋል፡፡

የክልሉ ኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ደምሰው ባቾሬ በበኩላቸው በአካባቢ ብክለት ምክንያት የሚከሰትን ሁለንተናዊ ጫና ለመከላከል በኢንቨስትመንት ዘርፉ የሚስተዋሉ ውስንነቶችን ለማረም ቢሮው በትኩረት እየሰራ ነው ብለዋል፡፡
በዚህም ለአዳዲስ ኢንቨስትመንቶች የአካባቢ ብክለትን መከላከል በሚያስችል መልኩ በክላስተር መሬት የማዘጋጀት ስራ መሰራቱንም ጠቅሰዋል፡፡

በዞኑ የሚከናወን የትኛውም የልማት ስራ የአካባቢንና የማህበረሰቡን ጤና ማስጠበቅን ማዕከል ያደረገ እንዲሆን ትኩረት መሰጠቱን የገለጹት ደግሞ የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዘይኔ ቢልካ ናቸው፡፡
ዞኑን የኢንዱስትሪና የአገልግሎት ማዕከል ለማድረግ በተሰጠው ትኩረት በርካታ ባለሀብቶች ዘርፉን እየተቀላቀሉ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

የደስታ ጋርመንት ዋና ስራ አስኪያጅ ያሬድ ወልዴ በበኩላቸው ከፋብሪካው የሚወገዱ ተረፈ ምርቶች አካባቢን እንዳይበክሉ መልሶ ጥቅም ላይ እንዲውሉ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በመርሃ ግብሩ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮችና በተለያየ ኢንቨስትመንት ዘርፍ የተሰማሩ ባለሃብቶች የተሳተፉ ሲሆን የፅዳት ዘመቻና የችግኝ ተከላ መርሐ ግብርም አከናውነዋል፡፡
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026