
አዲስ አበባ፤ሰኔ 3/2017(ኢዜአ)፦በአዲስ አበባ ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የተለያዩ የልማት ስራዎች የሚያስደንቁ መሆናቸውን የአርሜንያ ሪፐብሊክ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቫሃን ኮስታኒያን ገለጹ፡፡
ኢትዮጵያ እና አርመኒያ ያላቸው የረጅም ጊዜ ግንኙነትን ይበልጥ ለማጠናከር የሚያስችሉ ተግባራት እንደሚከናወኑም ገልጸዋል።
የአርሜንያ ሪፐብሊክ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቫሃን ኮስታኒያን ዛሬ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል፡፡
ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቫሃን ኮስታኒያን እንደገለጹት፤ አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የተመለከቷቸው ትልልቅ የልማት ስራዎችና ግንባታዎች የሚስደንቁና የከተማዋን ዓለምአቀፍ ተወዳዳሪነት የሚያሳድጉ ናቸው፡፡
የኢትዮጵያ ህዝብ ሰው ወዳድ፣ እንግዳ ተቀባይ ነው ያሉት ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኮስታኒያን፤ በኢትዮጵያ ቆይታቸው መልካም ጊዜ ማሳለፋቸውን ገልጸዋል፡፡
አርመኒያ ትምህርት፣ቴክኖሎጂ እና ጤና ከፍተኛ እውቅና ያገኘችባቸው ዘርፎች መሆናቸውን ጠቁመው፤ በእነኚህ እና በሌሎችም ዘርፎች ያላትን ልምድ ለኢትዮጵያ ለማካፈል ዝግጁ መሆኗን ተናግረዋል፡፡
በሌላ መልኩም በዲጂታላይዜሽን እና የመንግስት አገልግሎትን በቴክኖሎጂ ከመደገፍ አኳያም ከኢትዮጵያ ጋር በጋራ ለመሥራት ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
የኢትዮጵያ እና አርመኒያ የሁለትዮሽ ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናክር እንደሚሰሩም ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ቫሃን ኮስታኒያን ተናግረዋል፡፡
አርመኒያ ከኢትዮጵያ ጋራ ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኗን ጠቁመው፤ በኢትዮጵያ በኩልም ይህንን ቁርጠኝነት መመልከታቸውን ጠቁመዋል፡፡
አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...
Sep 14, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026