የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በአዲስ አበባ ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የተለያዩ የልማት ስራዎች የሚያስደንቁ ናቸው -ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቫሃን ኮስታኒያን

Jun 11, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሰኔ 3/2017(ኢዜአ)፦በአዲስ አበባ ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የተለያዩ የልማት ስራዎች የሚያስደንቁ መሆናቸውን የአርሜንያ ሪፐብሊክ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቫሃን ኮስታኒያን ገለጹ፡፡


ኢትዮጵያ እና አርመኒያ ያላቸው የረጅም ጊዜ ግንኙነትን ይበልጥ ለማጠናከር የሚያስችሉ ተግባራት እንደሚከናወኑም ገልጸዋል።


የአርሜንያ ሪፐብሊክ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቫሃን ኮስታኒያን ዛሬ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል፡፡


ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቫሃን ኮስታኒያን እንደገለጹት፤ አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የተመለከቷቸው ትልልቅ የልማት ስራዎችና ግንባታዎች የሚስደንቁና የከተማዋን ዓለምአቀፍ ተወዳዳሪነት የሚያሳድጉ ናቸው፡፡


የኢትዮጵያ ህዝብ ሰው ወዳድ፣ እንግዳ ተቀባይ ነው ያሉት ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኮስታኒያን፤ በኢትዮጵያ ቆይታቸው መልካም ጊዜ ማሳለፋቸውን ገልጸዋል፡፡


አርመኒያ ትምህርት፣ቴክኖሎጂ እና ጤና ከፍተኛ እውቅና ያገኘችባቸው ዘርፎች መሆናቸውን ጠቁመው፤ በእነኚህ እና በሌሎችም ዘርፎች ያላትን ልምድ ለኢትዮጵያ ለማካፈል ዝግጁ መሆኗን ተናግረዋል፡፡


በሌላ መልኩም በዲጂታላይዜሽን እና የመንግስት አገልግሎትን በቴክኖሎጂ ከመደገፍ አኳያም ከኢትዮጵያ ጋር በጋራ ለመሥራት ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡


የኢትዮጵያ እና አርመኒያ የሁለትዮሽ ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናክር እንደሚሰሩም ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ቫሃን ኮስታኒያን ተናግረዋል፡፡


አርመኒያ ከኢትዮጵያ ጋራ ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኗን ጠቁመው፤ በኢትዮጵያ በኩልም ይህንን ቁርጠኝነት መመልከታቸውን ጠቁመዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የአፍሪካ የልማትና ትብብር ዓርማ - ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በታዋቂው ታይም መጽሔት ገጽ

አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...

Sep 14, 2026

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026