
አዲስ አበባ፤ሰኔ 3/2017(ኢዜአ)፦በአዲስ አበባ ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የተለያዩ የልማት ስራዎች የሚያስደንቁ መሆናቸውን የአርሜንያ ሪፐብሊክ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቫሃን ኮስታኒያን ገለጹ፡፡
ኢትዮጵያ እና አርመኒያ ያላቸው የረጅም ጊዜ ግንኙነትን ይበልጥ ለማጠናከር የሚያስችሉ ተግባራት እንደሚከናወኑም ገልጸዋል።
የአርሜንያ ሪፐብሊክ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቫሃን ኮስታኒያን ዛሬ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል፡፡
ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቫሃን ኮስታኒያን እንደገለጹት፤ አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የተመለከቷቸው ትልልቅ የልማት ስራዎችና ግንባታዎች የሚስደንቁና የከተማዋን ዓለምአቀፍ ተወዳዳሪነት የሚያሳድጉ ናቸው፡፡
የኢትዮጵያ ህዝብ ሰው ወዳድ፣ እንግዳ ተቀባይ ነው ያሉት ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኮስታኒያን፤ በኢትዮጵያ ቆይታቸው መልካም ጊዜ ማሳለፋቸውን ገልጸዋል፡፡
አርመኒያ ትምህርት፣ቴክኖሎጂ እና ጤና ከፍተኛ እውቅና ያገኘችባቸው ዘርፎች መሆናቸውን ጠቁመው፤ በእነኚህ እና በሌሎችም ዘርፎች ያላትን ልምድ ለኢትዮጵያ ለማካፈል ዝግጁ መሆኗን ተናግረዋል፡፡
በሌላ መልኩም በዲጂታላይዜሽን እና የመንግስት አገልግሎትን በቴክኖሎጂ ከመደገፍ አኳያም ከኢትዮጵያ ጋር በጋራ ለመሥራት ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
የኢትዮጵያ እና አርመኒያ የሁለትዮሽ ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናክር እንደሚሰሩም ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ቫሃን ኮስታኒያን ተናግረዋል፡፡
አርመኒያ ከኢትዮጵያ ጋራ ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኗን ጠቁመው፤ በኢትዮጵያ በኩልም ይህንን ቁርጠኝነት መመልከታቸውን ጠቁመዋል፡፡
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026