የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በመዲናዋ የተገነቡ ሁለገብ የገበያ ማዕከላት የኑሮ ውድነት እና የዋጋ ንረትን በመቀነስ ረገድ ጉልህ አስተዋጽዎ እያበረከቱ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

Jun 11, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2017(ኢዜአ)፦በመዲናዋ የተገነቡ ሁለገብ የገበያ ማዕከላት የኑሮ ውድነት እና የዋጋ ንረትን በመቀነስ ረገድ ጉልህ አስተዋጽዎ እያበረከቱ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) የላፍቶ ቁጥር ሁለት ሁለገብ የገበያ ማዕከል ዛሬ መርቀው ስራ አስጀምረዋል።


ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት እንዳሉት በከተማዋ በተለያዩ አካባቢዎች የተገነቡ የገበያ ማዕከላት አምራቹንና ሸማቹን እንደ ድልድይ ሆኖ በቀጥታ በማገናኘት የኑሮ ውድነቱን እና የዋጋ ንረትን በመቀነስ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑን ተናግረዋል።

በዚህም ዛሬ የተመረቀው የላፍቶ ቁጥር 2 የገበያ ማዕከልም አምራቹንና ሸማቹ በቀጥታ በማገናኘት የኑሮ ውድነቱን እና የዋጋ ንረትን በመቀነስ የነዋሪዎችን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል።

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ህብረተሰቡ ጥራታቸውን የጠበቁ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኝና የኑሮ ውድነቱን ለመቀነስ የገበያ መሰረተ ልማቶችን የማስፋት ስራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም ተናግረዋል።


እንደሀገር መንግስት የኑሮ ውድነትን ለማቃለል በርካታ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ በመግለጽ፤ የቅዳሜ እና እሁድ ገበያዎችን በማስፋት ተጨባጭ ለውጦች መምጣታቸውን ተናግረዋል፡፡

በሀገሪቱ የንግድ ስርዓት ማሻሻል ለዘርፉ መሰረታዊ ለውጥ ወሳኝ መሆኑን በመገንዘብ መንግስት በከፍተኛ ትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ የገለጹ ሲሆን መሰል የገበያ ማእከሎች የኑሮ ውድነቱን በማረጋጋት በኩል አይነተኛ ሚና እንዳለቸው አብራርተዋል፡፡


የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ኃላፊ ሃቢባ ሲራጅ በበኩላቸው፤ በከተማዋ በሁሉም አካባቢዎች የተገነቡት የገበያ ማእከላት በርካታ ጥቅሞችን ለነዋሪው እና ለአምራቹም ጭምር እያበረከቱ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በተለይም የተገነቡት ማእከላት አምራችና ሸማቹን በቀጥታ እንዲገበያዩ በማስቻል በኩል ከፍተኛ ጠቀሜታ እያበረከቱ መሆኑን አንስተዋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ ዲዛይንና ግንባታ ሥራዎች ቢሮ ሃላፊ ኢንጅነር አያልነሽ ሃብተማሪያም በበኩላቸው፤ ማዕከሉ አገልግሎት እንዲሰጥ የታሰበውን ዘመናዊና የተደራጀ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችሉ በርካታ መሰረተ ልማት የተሟሉለት መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የላፍቶ ቁጥር 2 የምርት ግብይት ማዕከልም በ8 ነጥብ 8 ሄክታር ላይ የተገነባ፣ 159 ሰፋፊና ምቹ ሱቆችን፣ 9 የጅምላ ማከፋፊያዎች እና 2 ሞሎችን የያዘ ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026