
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2017(ኢዜአ)፦ የንግዱ ማህበረሰብ የትናንት ስብራቷ የተጠገነ እና ነገዋ የተሰራ ኢትዮጵያን ለቀጣዩ ትውልድ የማስረከብ ስራ ላይ ትልቅ ኃላፊነት እንዳለበት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከመላው ኢትዮጵያ ከተውጣጡ የንግድ ማህበረሰብ ተወካዮች ጋር ውይይት አድርገዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ገበያ እና ንግድ ለአንድ ሀገር እድገት ከፍተኛ ድርሻ እንዳላቸው ገልጸዋል።
ገበያ ሀገር ይገነባል፣ ገበያ እውቀት ያሸጋግራል፣ ገበያ ስልጣኔ ያመጣል እንዲሁም ገበያ የአኗኗር ዘይቤን ይቀይራል ብለዋል።
ገበያ ብር የሚገኝበት ብቻ አይደለም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሀገር የሚገነባበት እና ለአንድ ሀገር ህልውና ወሳኝ ሚና ያለው መሆኑን ገልጸዋል።
በዚህ ረገድም የንግዱ ማህበረሰብ ካለው ሰፊ ተደራሽነት አንጻር በሀገር ግንባታ እና እድገት ላይ ጉልህ ድርሻ አለው ነው ያሉት።

ኢትዮጵያ የከረሙ እና አዲስ ፈተናዎች ያለባት ሀገር መሆኗን ገልጸው የከረሙ ፈተናዎች ፈትቶ የወደፊቱ ላይ መስራት ካልተቻለ ትውልድ የተጠገነ ትናትና ያልተሰራ ነገን ስለሚረከብ መከራው እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
ያለፈውን መጠገንና የመጪውን የመሽቀዳደም ዘመን ሚዛን ጠብቆ መሄድን ከግምት ውስጥ ማስገባት እንደሚገባም ነው ያስረዱት።
ኢትዮጵያውያን ከዕለት ጉዳዮቻችን ባለፈ በዋና ሀገራዊ ጉዳዮችና ፈተናዎቻችን ላይ የመምከር ባህላችን መሻሻል እንደሚያስፈልገውም አንስተዋል።
በነገ የሀገር እጣ ፈንታ ያለመምከር ችግር በሁሉም ዘርፍ የሚታይ ጉዳይ ነው ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።

የንግዱ ማህበረሰብ ባለው ሰፊ አቅም እና ተደራሽነት ያለፉ ችግሮችን የመፍታትና ነገን የመገንባት ስራ ላይ ማህበረሰቡን የማስተማርና የማንቃት ላይ ስራ እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርበዋል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026