
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2017(ኢዜአ)፦ የንግዱ ማህበረሰብ የትናንት ስብራቷ የተጠገነ እና ነገዋ የተሰራ ኢትዮጵያን ለቀጣዩ ትውልድ የማስረከብ ስራ ላይ ትልቅ ኃላፊነት እንዳለበት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከመላው ኢትዮጵያ ከተውጣጡ የንግድ ማህበረሰብ ተወካዮች ጋር ውይይት አድርገዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ገበያ እና ንግድ ለአንድ ሀገር እድገት ከፍተኛ ድርሻ እንዳላቸው ገልጸዋል።
ገበያ ሀገር ይገነባል፣ ገበያ እውቀት ያሸጋግራል፣ ገበያ ስልጣኔ ያመጣል እንዲሁም ገበያ የአኗኗር ዘይቤን ይቀይራል ብለዋል።
ገበያ ብር የሚገኝበት ብቻ አይደለም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሀገር የሚገነባበት እና ለአንድ ሀገር ህልውና ወሳኝ ሚና ያለው መሆኑን ገልጸዋል።
በዚህ ረገድም የንግዱ ማህበረሰብ ካለው ሰፊ ተደራሽነት አንጻር በሀገር ግንባታ እና እድገት ላይ ጉልህ ድርሻ አለው ነው ያሉት።

ኢትዮጵያ የከረሙ እና አዲስ ፈተናዎች ያለባት ሀገር መሆኗን ገልጸው የከረሙ ፈተናዎች ፈትቶ የወደፊቱ ላይ መስራት ካልተቻለ ትውልድ የተጠገነ ትናትና ያልተሰራ ነገን ስለሚረከብ መከራው እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
ያለፈውን መጠገንና የመጪውን የመሽቀዳደም ዘመን ሚዛን ጠብቆ መሄድን ከግምት ውስጥ ማስገባት እንደሚገባም ነው ያስረዱት።
ኢትዮጵያውያን ከዕለት ጉዳዮቻችን ባለፈ በዋና ሀገራዊ ጉዳዮችና ፈተናዎቻችን ላይ የመምከር ባህላችን መሻሻል እንደሚያስፈልገውም አንስተዋል።
በነገ የሀገር እጣ ፈንታ ያለመምከር ችግር በሁሉም ዘርፍ የሚታይ ጉዳይ ነው ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።

የንግዱ ማህበረሰብ ባለው ሰፊ አቅም እና ተደራሽነት ያለፉ ችግሮችን የመፍታትና ነገን የመገንባት ስራ ላይ ማህበረሰቡን የማስተማርና የማንቃት ላይ ስራ እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርበዋል።
አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...
Sep 14, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026