
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2017(ኢዜአ)፦ የንግዱ ማህበረሰብ የትናንት ስብራቷ የተጠገነ እና ነገዋ የተሰራ ኢትዮጵያን ለቀጣዩ ትውልድ የማስረከብ ስራ ላይ ትልቅ ኃላፊነት እንዳለበት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከመላው ኢትዮጵያ ከተውጣጡ የንግድ ማህበረሰብ ተወካዮች ጋር ውይይት አድርገዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ገበያ እና ንግድ ለአንድ ሀገር እድገት ከፍተኛ ድርሻ እንዳላቸው ገልጸዋል።
ገበያ ሀገር ይገነባል፣ ገበያ እውቀት ያሸጋግራል፣ ገበያ ስልጣኔ ያመጣል እንዲሁም ገበያ የአኗኗር ዘይቤን ይቀይራል ብለዋል።
ገበያ ብር የሚገኝበት ብቻ አይደለም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሀገር የሚገነባበት እና ለአንድ ሀገር ህልውና ወሳኝ ሚና ያለው መሆኑን ገልጸዋል።
በዚህ ረገድም የንግዱ ማህበረሰብ ካለው ሰፊ ተደራሽነት አንጻር በሀገር ግንባታ እና እድገት ላይ ጉልህ ድርሻ አለው ነው ያሉት።

ኢትዮጵያ የከረሙ እና አዲስ ፈተናዎች ያለባት ሀገር መሆኗን ገልጸው የከረሙ ፈተናዎች ፈትቶ የወደፊቱ ላይ መስራት ካልተቻለ ትውልድ የተጠገነ ትናትና ያልተሰራ ነገን ስለሚረከብ መከራው እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
ያለፈውን መጠገንና የመጪውን የመሽቀዳደም ዘመን ሚዛን ጠብቆ መሄድን ከግምት ውስጥ ማስገባት እንደሚገባም ነው ያስረዱት።
ኢትዮጵያውያን ከዕለት ጉዳዮቻችን ባለፈ በዋና ሀገራዊ ጉዳዮችና ፈተናዎቻችን ላይ የመምከር ባህላችን መሻሻል እንደሚያስፈልገውም አንስተዋል።
በነገ የሀገር እጣ ፈንታ ያለመምከር ችግር በሁሉም ዘርፍ የሚታይ ጉዳይ ነው ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።

የንግዱ ማህበረሰብ ባለው ሰፊ አቅም እና ተደራሽነት ያለፉ ችግሮችን የመፍታትና ነገን የመገንባት ስራ ላይ ማህበረሰቡን የማስተማርና የማንቃት ላይ ስራ እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርበዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026