
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 5/2017(ኢዜአ)፦ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ለማሳያነት ያስገነባው 100 ኪሎ ዋት የሚያመነጭ የሶላር ፕሮጀክት ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።
የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር) የሶላር ፕሮጀክቱን መርቀው ስራ አስጀምረዋል።
ሚኒስትሩ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት በአገሪቱ ኢነርጂን ለማስፋፋት በተሰሩ ስራዎች በአገሪቱ የሀይል አቅርቦትን በማስፋፋት በርካታ የማህበረሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል።
በሚኒስቴሩ ግቢ ውስጥ የተገነባው የሶላር ኢነርጂ በከተማ ተግባራዊ ማድረግ እንደሚቻል ማሳያ ነው ብለዋል።
ሶላር ኢነርጂው የተቋሙን ሀይል ከመሸፈን በተጨማሪ ወደ ዋና ግሬድ በመግባት ለሌሎች ሀይል መስጠት የሚችል መሆኑን ተናግረዋል።
የተመረቀው የሶላር ኢነርጂ ባለሀብቶች የራሳቸውን ሀይል አመንጭተው እንዲጠቀሙ ምሳሌ የሚሆን ፕሮጀክት መሆኑን አስታውቀዋል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026