
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 5/2017(ኢዜአ)፦ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ለማሳያነት ያስገነባው 100 ኪሎ ዋት የሚያመነጭ የሶላር ፕሮጀክት ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።
የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር) የሶላር ፕሮጀክቱን መርቀው ስራ አስጀምረዋል።
ሚኒስትሩ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት በአገሪቱ ኢነርጂን ለማስፋፋት በተሰሩ ስራዎች በአገሪቱ የሀይል አቅርቦትን በማስፋፋት በርካታ የማህበረሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል።
በሚኒስቴሩ ግቢ ውስጥ የተገነባው የሶላር ኢነርጂ በከተማ ተግባራዊ ማድረግ እንደሚቻል ማሳያ ነው ብለዋል።
ሶላር ኢነርጂው የተቋሙን ሀይል ከመሸፈን በተጨማሪ ወደ ዋና ግሬድ በመግባት ለሌሎች ሀይል መስጠት የሚችል መሆኑን ተናግረዋል።
የተመረቀው የሶላር ኢነርጂ ባለሀብቶች የራሳቸውን ሀይል አመንጭተው እንዲጠቀሙ ምሳሌ የሚሆን ፕሮጀክት መሆኑን አስታውቀዋል።
አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...
Sep 14, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026