
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 5/2017(ኢዜአ)፦ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ለማሳያነት ያስገነባው 100 ኪሎ ዋት የሚያመነጭ የሶላር ፕሮጀክት ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።
የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር) የሶላር ፕሮጀክቱን መርቀው ስራ አስጀምረዋል።
ሚኒስትሩ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት በአገሪቱ ኢነርጂን ለማስፋፋት በተሰሩ ስራዎች በአገሪቱ የሀይል አቅርቦትን በማስፋፋት በርካታ የማህበረሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል።
በሚኒስቴሩ ግቢ ውስጥ የተገነባው የሶላር ኢነርጂ በከተማ ተግባራዊ ማድረግ እንደሚቻል ማሳያ ነው ብለዋል።
ሶላር ኢነርጂው የተቋሙን ሀይል ከመሸፈን በተጨማሪ ወደ ዋና ግሬድ በመግባት ለሌሎች ሀይል መስጠት የሚችል መሆኑን ተናግረዋል።
የተመረቀው የሶላር ኢነርጂ ባለሀብቶች የራሳቸውን ሀይል አመንጭተው እንዲጠቀሙ ምሳሌ የሚሆን ፕሮጀክት መሆኑን አስታውቀዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026