የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በኢትዮጵያ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት የበኩሉን ሚና እየተወጣ ይገኛል

Jun 13, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 5/2017(ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ ዘላቂ የልማት ግቦችን ለማሳካት እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራትን ለማጠናከር የበኩሉን ሚና እየተወጣ እንደሚገኝ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አስታወቀ።


በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የትምህርትና ቋንቋዎች ጥናት ኮሌጅ "ጥራት ያለው ትምህርት ለኢትዮጵያ ዘላቂ ልማት" በሚል መሪ ሃሳብ የትምህርት ጥራትና ፍትሃዊነትን በሚመለከት ውይይት ተካሂዷል፡፡


ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግስታት የ2030 ዘላቂ የልማት አጀንዳ አካል የሆነውን የትምህርት ጥራትና ፍትሃዊነትን የማረጋገጥ ግብን ለማሳካት በርካታ ተግባራትን ማከናወኗ በመድረኩ ተገልጿል፡፡


ከዚህ አኳያ ያስመዘገበቻቸውን ስኬቶች ለማስቀጠልና የገጠሙ ተግዳሮቶችን በመፍታት ግቡን ሙሉ በሙሉ ለማሳካት በሚቻልበት ሁኔታ ዙሪያ ምክክር ተደርጓል።


የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) እንደገለጹት፥ ዩኒቨርሲቲው ለዘላቂ የልማት ግቦች ስኬት የሚጠበቅበትን እያበረከተ ነው፡፡


በዚህም ችግር ፈቺ ጥናትና ምርምሮችን እንዲሁም የፈጠራ ሥራና የማህበረሰብ አገልግሎት በማከናወን ለግቡ ስኬት የበኩሉን እየተወጣ መሆኑን ተናግረዋል።


ዩኒቨርሲቲው ግቦቹን በስትራቴጂክ ዕቅዱ በማካተት ለስኬቱ እየሰራ እንደሚገኝ ጠቅሰው፥ ዘላቂ የልማት ግቦችን ውጤታማ ለማድረግ የትምህርት ጥራትን ማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡


የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ ምክትል ፕሬዝዳንት ጀይሉ ኡመር (ዶ/ር) በበኩላቸው ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ለዘላቂ የልማት ግቦች ስኬት ትልቅ ሚና እንዳላቸው ተናግረዋል፡፡


ለዚህም የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ጥራትን በማረጋገጥና ተደራሽነትን በማስፋት ለግቡ ስኬት ወሳኝ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡


በዩኒቨርሲቲው የትምህርትና ቋንቋዎች ጥናት ኮሌጅ ኤክስኪዩቲቭ ዲን የቆየዓለም ደሴ (ዶ/ር) ፥ የትምህርትን ዘላቂ የልማት ግብ ለማሳካት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሚና፣ ትምህርትን በፋይናንስ መደገፍና ወቅታዊ አተገባበርን በተመለከተ ጽሑፎች ቀርበው ውይይት እንደተካሄደባቸው ገልጸዋል፡፡


ዩኒቨርሲቲው ለዘላቂ የልማት ግቡ ስኬት የተለያዩ ጥናትና ምርምሮችን በማካሄድ ላይ እንደሚገኝም ጠቁመዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የአፍሪካ የልማትና ትብብር ዓርማ - ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በታዋቂው ታይም መጽሔት ገጽ

አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...

Sep 14, 2026

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026