የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ኢትዮጵያ ወደ ቻይና የምትልካቸውን ምርቶች በአይነትና በመጠን ለማሳደግ የሚያስችሉ ስራዎች እየተከናወኑ ነው-አምባሳደር ተፈራ ደርበው

Jun 13, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሰኔ 5/2017 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ወደ ቻይና የምትልካቸውን ምርቶች በአይነትም በመጠን ለማሳደግ የሚያስችሉ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን በቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር ተፈራ ደርበው ገለጹ።

አራተኛው የቻይና አፍሪካ የኢኮኖሚና ንግድ ኤክስፖ በቻይና ቻንግሻ ከተማ ዛሬ ተከፍቷል።

ከኤክስፖው ጎን ለጎንም የኢትዮጵያን የአኩሪ አተር ተረፈ ምርት በቻይና ለማቅረብ የሚያስችል ስምምነት መፈረሙን የኢዜአ ሪፖርተር ከስፍራው ዘግቧል።

ስምምነቱን በቻይና የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ተፈራ ደርበውና የቻይና የጉምሩክ አጠቃላይ አስተዳደር ምክትል ሚኒስትር ዋንግ ልንግጁን ተፈራርመውታል።

አምባሳደሩ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ስምምነቱ ለኢትዮጵያ አዲስ የገበያ እድል ከማስገኘቱ በተጨማሪ ወደ ቻይና የሚላኩ ምርቶችን መጠን ከፍ የሚያደርግ ነው።

ስምምነቱ ባለፉት ስድስት ወራት በኢትዮጵያ የግብርና ባለስልጣንና በቻይና ጉምሩክ ባለስልጣን በጋራ ሲዘጋጅ መቆየቱን አንስተዋል።

ስምምነቱ ከሀገሪቱ ጋር ያለውን የንግድ ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር እንደሚረዳ ገልጸው፤ኢትዮጵያ ወደ ቻይና የምትልካቸውን ምርቶች በአይነትም በመጠንም ለማሳደግ የሚያስችሉ ስራዎች እየተከናወኑ ነው ብለዋል።

በተመሳሳይም አምባሳደር ተፈራ 'ከቻንግሻ ሳተርንበርድ ኮፊ ኤልቲዲ' (Changsha Saturnbird Coffee Co.,LTD.) መስራች እና ሊቀመንበር ሚስተር ው ጁን ጋር የኢትዮጵያ ቡናን እሴት ጨምሮ ለቻይና ገበያ ለማቅረብ እንዲችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል።

ኩባንያው የኢትዮጵያ ቡናን በብዛት በመግዛት ለሌሎች የቻይና ቡና ኩባንያዎች ለማከፋፈል፣ ቆልቶ ለማዘጋጀት፣ለመፍጨት እና የቡና ምርቶች ለማዘጋጀት እንደግብዓት የሚጠቀም መሆኑ ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢንዱስትሪ ፓርኩ መገንባት መንግሥት ለዘርፉ የሰጠውን ትኩረት በተጨባጭ ያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...

May 20, 2026

የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል 

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...

May 7, 2026

የከተማዋን ባህል፣ ታሪክ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በማልማት ለኢኮኖሚያዊ ጥቅም የማዋል ተግባራት ይጠናከራሉ

ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...

May 7, 2026

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026