
አዲስ አበባ፤ሰኔ 5/2017 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ወደ ቻይና የምትልካቸውን ምርቶች በአይነትም በመጠን ለማሳደግ የሚያስችሉ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን በቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር ተፈራ ደርበው ገለጹ።
አራተኛው የቻይና አፍሪካ የኢኮኖሚና ንግድ ኤክስፖ በቻይና ቻንግሻ ከተማ ዛሬ ተከፍቷል።
ከኤክስፖው ጎን ለጎንም የኢትዮጵያን የአኩሪ አተር ተረፈ ምርት በቻይና ለማቅረብ የሚያስችል ስምምነት መፈረሙን የኢዜአ ሪፖርተር ከስፍራው ዘግቧል።
ስምምነቱን በቻይና የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ተፈራ ደርበውና የቻይና የጉምሩክ አጠቃላይ አስተዳደር ምክትል ሚኒስትር ዋንግ ልንግጁን ተፈራርመውታል።
አምባሳደሩ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ስምምነቱ ለኢትዮጵያ አዲስ የገበያ እድል ከማስገኘቱ በተጨማሪ ወደ ቻይና የሚላኩ ምርቶችን መጠን ከፍ የሚያደርግ ነው።
ስምምነቱ ባለፉት ስድስት ወራት በኢትዮጵያ የግብርና ባለስልጣንና በቻይና ጉምሩክ ባለስልጣን በጋራ ሲዘጋጅ መቆየቱን አንስተዋል።
ስምምነቱ ከሀገሪቱ ጋር ያለውን የንግድ ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር እንደሚረዳ ገልጸው፤ኢትዮጵያ ወደ ቻይና የምትልካቸውን ምርቶች በአይነትም በመጠንም ለማሳደግ የሚያስችሉ ስራዎች እየተከናወኑ ነው ብለዋል።
በተመሳሳይም አምባሳደር ተፈራ 'ከቻንግሻ ሳተርንበርድ ኮፊ ኤልቲዲ' (Changsha Saturnbird Coffee Co.,LTD.) መስራች እና ሊቀመንበር ሚስተር ው ጁን ጋር የኢትዮጵያ ቡናን እሴት ጨምሮ ለቻይና ገበያ ለማቅረብ እንዲችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል።
ኩባንያው የኢትዮጵያ ቡናን በብዛት በመግዛት ለሌሎች የቻይና ቡና ኩባንያዎች ለማከፋፈል፣ ቆልቶ ለማዘጋጀት፣ለመፍጨት እና የቡና ምርቶች ለማዘጋጀት እንደግብዓት የሚጠቀም መሆኑ ተገልጿል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026