
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 12/2017(ኢዜአ)፦ መንግስት ለአምራች ኢንዱስትሪዎች ምቹ መደላድል እየፈጠረ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ 26 ለሚሆኑ አምራች ኢንዱስትሪዎች የመስሪያ ቦታ አስረክበዋል።

የመስሪያ ቦታ ከተሰጣቸው መካከል 15ቱ አምራች ኢንዱስትሪዎች አዲስ የመስሪያ ቦታ ቁልፍ የተሰጣቸው ናቸው።
በዚህ ወቅት ከንቲባ አዳነች መንግስት የአምራች ኢንዱስትሪዎች በሚፈለገው ልክ አቅማቸውን ተጠቅመው ምርትና ምርታማነታቸውን እንዲያሳድጉ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች ምቹ መደላድል የመፍጠር ስራ በትኩረት እያከናወነ ይገኛል ብለዋል።
የዘርፉ ተዋናዮች ከሚያነሷቸው አንኳር ጥያቄዎች መካከል የመስሪያ ቦታ መሆኑን አንስተው፤ ከዚህ ጋር ተያይዞ የሚነሱ ጥያቄዎች አግባብነትን ከተማ አስተዳደሩ በመፈተሽ ደረጃ በደረጃ መፍትሄ እንዲያገኙ እያደረገ መሆኑን ጠቅሰዋል።
በዛሬው ዕለትም ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው የመስሪያ ቦታ ርክክብ አንዱ ማሳያ መሆኑን በመጠቆም።
እንደ ሀገር ትልቁ የእድገታችን ማነቆ ድህነት መሆኑን ገልጸው፤ ይህን ለመፍታት አምራች ኢንዱስትሪዎች ያላቸውን እምቅ ሀብትና ጊዜ በአግባቡ በመጠቀም ውጤታማ እንዲሆኑ አሳስበዋል።
ከተማ አስተዳደሩም በቀጣይ አምራች ኢንዱስትሪዎች በሚያመርቱት ምርት ተወዳዳሪ እንዲሆኑ አስፈላጊውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ እና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ሃላፊ ጃንጥራር አባይ በበኩላቸው፤ ከተማ አስተዳደሩ የከተማውን ውስን ሀብት የሆነውን መሬት ፍትሃዊ በሆነ መልኩ ጥቅም ላይ ለማዋል እየሰራ ነው ብለዋል።
አምራች ኢንዱስትሪዎች የመስሪያ ቦታን ፍላጎት መመለስ በሚያስችል አግባብ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው፤ በአሁኑ ወቅት በመዲናዋ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ እየተከናወነ ያለው የኢንዱስትሪ ክላስተር ልማት ይህን ፍላጎት ለመሙላት ጉልህ ድርሻ እንደሚኖረው ተናግረዋል።
በዛሬው እለት አዲስ የመስሪያ ቦታ ቁልፍ የተረከቡት መላ ፎር ኸር የሴቶች ንጽህና መጠበቂያ ማምረቻ ምክትል ስራ አስኪያጅ ኤርሚያስ ሲሳይ በበኩላቸው፤ ምርታቸውን በተረጋጋ የመስሪያ ቦታ ለማምረት አቅም እንደሚሰጣቸው ገልጸዋል።
ከተማ አስተዳደሩ የሰጣቸው የመስሪያ ቦታ ከፍተኛ የስራ ተነሳሽነታቸውን የሚያሳድግ መሆኑን ገልጸው፤ ለታለመለት ዓላማ ለማዋል ቁርጠኛ ነን ሲሉ አክለዋል።
የመስሪያ ቦታ ቁልፍ በመረከባቸው ደስተኛ መሆናቸውን ጠቁመው፤ ለስራቸው የሚረዱ አዳዲስ ማሽነሪዎችን በማስገባት ተኪ ምርቶችን በስፋት ለማምረት ያግዘናል ያሉት ደግሞ የብራዘርስ ጋርመንት ስራ አስኪያጅ ነጻነት መቻል ናቸው።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026