
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 12/2017(ኢዜአ)፦ መንግስት ለአምራች ኢንዱስትሪዎች ምቹ መደላድል እየፈጠረ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ 26 ለሚሆኑ አምራች ኢንዱስትሪዎች የመስሪያ ቦታ አስረክበዋል።

የመስሪያ ቦታ ከተሰጣቸው መካከል 15ቱ አምራች ኢንዱስትሪዎች አዲስ የመስሪያ ቦታ ቁልፍ የተሰጣቸው ናቸው።
በዚህ ወቅት ከንቲባ አዳነች መንግስት የአምራች ኢንዱስትሪዎች በሚፈለገው ልክ አቅማቸውን ተጠቅመው ምርትና ምርታማነታቸውን እንዲያሳድጉ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች ምቹ መደላድል የመፍጠር ስራ በትኩረት እያከናወነ ይገኛል ብለዋል።
የዘርፉ ተዋናዮች ከሚያነሷቸው አንኳር ጥያቄዎች መካከል የመስሪያ ቦታ መሆኑን አንስተው፤ ከዚህ ጋር ተያይዞ የሚነሱ ጥያቄዎች አግባብነትን ከተማ አስተዳደሩ በመፈተሽ ደረጃ በደረጃ መፍትሄ እንዲያገኙ እያደረገ መሆኑን ጠቅሰዋል።
በዛሬው ዕለትም ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው የመስሪያ ቦታ ርክክብ አንዱ ማሳያ መሆኑን በመጠቆም።
እንደ ሀገር ትልቁ የእድገታችን ማነቆ ድህነት መሆኑን ገልጸው፤ ይህን ለመፍታት አምራች ኢንዱስትሪዎች ያላቸውን እምቅ ሀብትና ጊዜ በአግባቡ በመጠቀም ውጤታማ እንዲሆኑ አሳስበዋል።
ከተማ አስተዳደሩም በቀጣይ አምራች ኢንዱስትሪዎች በሚያመርቱት ምርት ተወዳዳሪ እንዲሆኑ አስፈላጊውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ እና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ሃላፊ ጃንጥራር አባይ በበኩላቸው፤ ከተማ አስተዳደሩ የከተማውን ውስን ሀብት የሆነውን መሬት ፍትሃዊ በሆነ መልኩ ጥቅም ላይ ለማዋል እየሰራ ነው ብለዋል።
አምራች ኢንዱስትሪዎች የመስሪያ ቦታን ፍላጎት መመለስ በሚያስችል አግባብ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው፤ በአሁኑ ወቅት በመዲናዋ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ እየተከናወነ ያለው የኢንዱስትሪ ክላስተር ልማት ይህን ፍላጎት ለመሙላት ጉልህ ድርሻ እንደሚኖረው ተናግረዋል።
በዛሬው እለት አዲስ የመስሪያ ቦታ ቁልፍ የተረከቡት መላ ፎር ኸር የሴቶች ንጽህና መጠበቂያ ማምረቻ ምክትል ስራ አስኪያጅ ኤርሚያስ ሲሳይ በበኩላቸው፤ ምርታቸውን በተረጋጋ የመስሪያ ቦታ ለማምረት አቅም እንደሚሰጣቸው ገልጸዋል።
ከተማ አስተዳደሩ የሰጣቸው የመስሪያ ቦታ ከፍተኛ የስራ ተነሳሽነታቸውን የሚያሳድግ መሆኑን ገልጸው፤ ለታለመለት ዓላማ ለማዋል ቁርጠኛ ነን ሲሉ አክለዋል።
የመስሪያ ቦታ ቁልፍ በመረከባቸው ደስተኛ መሆናቸውን ጠቁመው፤ ለስራቸው የሚረዱ አዳዲስ ማሽነሪዎችን በማስገባት ተኪ ምርቶችን በስፋት ለማምረት ያግዘናል ያሉት ደግሞ የብራዘርስ ጋርመንት ስራ አስኪያጅ ነጻነት መቻል ናቸው።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026