
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 12/2017(ኢዜአ)፦ መንግስት ለአምራች ኢንዱስትሪዎች ምቹ መደላድል እየፈጠረ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ 26 ለሚሆኑ አምራች ኢንዱስትሪዎች የመስሪያ ቦታ አስረክበዋል።

የመስሪያ ቦታ ከተሰጣቸው መካከል 15ቱ አምራች ኢንዱስትሪዎች አዲስ የመስሪያ ቦታ ቁልፍ የተሰጣቸው ናቸው።
በዚህ ወቅት ከንቲባ አዳነች መንግስት የአምራች ኢንዱስትሪዎች በሚፈለገው ልክ አቅማቸውን ተጠቅመው ምርትና ምርታማነታቸውን እንዲያሳድጉ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች ምቹ መደላድል የመፍጠር ስራ በትኩረት እያከናወነ ይገኛል ብለዋል።
የዘርፉ ተዋናዮች ከሚያነሷቸው አንኳር ጥያቄዎች መካከል የመስሪያ ቦታ መሆኑን አንስተው፤ ከዚህ ጋር ተያይዞ የሚነሱ ጥያቄዎች አግባብነትን ከተማ አስተዳደሩ በመፈተሽ ደረጃ በደረጃ መፍትሄ እንዲያገኙ እያደረገ መሆኑን ጠቅሰዋል።
በዛሬው ዕለትም ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው የመስሪያ ቦታ ርክክብ አንዱ ማሳያ መሆኑን በመጠቆም።
እንደ ሀገር ትልቁ የእድገታችን ማነቆ ድህነት መሆኑን ገልጸው፤ ይህን ለመፍታት አምራች ኢንዱስትሪዎች ያላቸውን እምቅ ሀብትና ጊዜ በአግባቡ በመጠቀም ውጤታማ እንዲሆኑ አሳስበዋል።
ከተማ አስተዳደሩም በቀጣይ አምራች ኢንዱስትሪዎች በሚያመርቱት ምርት ተወዳዳሪ እንዲሆኑ አስፈላጊውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ እና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ሃላፊ ጃንጥራር አባይ በበኩላቸው፤ ከተማ አስተዳደሩ የከተማውን ውስን ሀብት የሆነውን መሬት ፍትሃዊ በሆነ መልኩ ጥቅም ላይ ለማዋል እየሰራ ነው ብለዋል።
አምራች ኢንዱስትሪዎች የመስሪያ ቦታን ፍላጎት መመለስ በሚያስችል አግባብ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው፤ በአሁኑ ወቅት በመዲናዋ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ እየተከናወነ ያለው የኢንዱስትሪ ክላስተር ልማት ይህን ፍላጎት ለመሙላት ጉልህ ድርሻ እንደሚኖረው ተናግረዋል።
በዛሬው እለት አዲስ የመስሪያ ቦታ ቁልፍ የተረከቡት መላ ፎር ኸር የሴቶች ንጽህና መጠበቂያ ማምረቻ ምክትል ስራ አስኪያጅ ኤርሚያስ ሲሳይ በበኩላቸው፤ ምርታቸውን በተረጋጋ የመስሪያ ቦታ ለማምረት አቅም እንደሚሰጣቸው ገልጸዋል።
ከተማ አስተዳደሩ የሰጣቸው የመስሪያ ቦታ ከፍተኛ የስራ ተነሳሽነታቸውን የሚያሳድግ መሆኑን ገልጸው፤ ለታለመለት ዓላማ ለማዋል ቁርጠኛ ነን ሲሉ አክለዋል።
የመስሪያ ቦታ ቁልፍ በመረከባቸው ደስተኛ መሆናቸውን ጠቁመው፤ ለስራቸው የሚረዱ አዳዲስ ማሽነሪዎችን በማስገባት ተኪ ምርቶችን በስፋት ለማምረት ያግዘናል ያሉት ደግሞ የብራዘርስ ጋርመንት ስራ አስኪያጅ ነጻነት መቻል ናቸው።
አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...
Sep 14, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026