አዲስ አበባ፤ ሰኔ 12/2017(ኢዜአ)፦ የደንበኞች አገልግሎትን በማዘመን የኤሌክትሪክ መቆራረጥ ለመቀነስና ፍትሃዊ ተደራሽነትን ለማረጋገጥ እየሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ገለጸ።
ተቋሙ አገልግሎቱን በማዘመን የኤሌክትሪክ መቆራረጥን ለመቀነስና ፍትሃዊ ተደራሽነትን ለማረጋገጥ በሚያደርገው ጥረት ቅንጅታዊ አሰራር መፍጠር የሚያስችል የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ጉብኝትና የሚዲያ ፎረም አካሂዷል።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የፕሮሰስና ጥራት ማኔጅመንት ስራ አስፈፃሚ እሱባለው ጤናው እንደገለጹት፤ የኤሌክትሪክ መቆራረጥን ለማስቀረት በዋነኝነት መሰረተ ልማቶች ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሰራ ነው።
ከተግባራቱ መካከል አገልግሎት አሰጣጡን በቴክኖሎጂ መደገፍ አንዱ መሆኑን አንስተው፤ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰዋል።
በዚህም ካሁን ቀደም በዘርፉ የነበሩ ተግዳሮቶች እየተሻሻሉ መምጣታቸውን ጠቁመዋል፡፡
የኤሌክትሪክ መቆራረጥን ለማስቀረት የተጀመረው ቴክኖሎጂን መሰረት ያደረገ አሰራር ማህበረሰቡ እንዲያውቀው ለማድረግና ብልሹ አሰራሮችን ለማጋለጥ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ሚና የላቀ ነው ብለዋል።
የአገልግሎቱ የኮሙኒኬሽን ዘርፍ ስራ አስፈፃሚ አንዋር አብራር በበኩላቸው፤ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማትን ከስርቆት ለመጠበቅ የማህበረሰቡ ተሳትፎ እንደሚያስፈልግ አንስተዋል።
መገናኛ ብዙሃንም በማህበረሰቡ ዘንድ ግንዛቤ ከመፍጠር አኳያ የበኩላቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ነው የተናገሩት፡፡
ለዚህም አገልግሎቱ ከመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ጋር ተቀራርቦ መስራት የሚያስችለውን ጉብኝት ማድረግና የሚድያ ፎረም ማቋቋም ማስፈለጉን ጠቅሰዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025
ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...
Feb 28, 2025
ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...
Feb 24, 2025