የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

የደንበኞች አገልግሎትን በማዘመን የኤሌክትሪክ መቆራረጥ ለመቀነስና ፍትሃዊ ተደራሽነትን ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው - አገልግሎቱ

Jun 20, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 12/2017(ኢዜአ)፦ የደንበኞች አገልግሎትን በማዘመን የኤሌክትሪክ መቆራረጥ ለመቀነስና ፍትሃዊ ተደራሽነትን ለማረጋገጥ እየሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ገለጸ።

ተቋሙ አገልግሎቱን በማዘመን የኤሌክትሪክ መቆራረጥን ለመቀነስና ፍትሃዊ ተደራሽነትን ለማረጋገጥ በሚያደርገው ጥረት ቅንጅታዊ አሰራር መፍጠር የሚያስችል የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ጉብኝትና የሚዲያ ፎረም አካሂዷል።


በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የፕሮሰስና ጥራት ማኔጅመንት ስራ አስፈፃሚ እሱባለው ጤናው እንደገለጹት፤ የኤሌክትሪክ መቆራረጥን ለማስቀረት በዋነኝነት መሰረተ ልማቶች ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሰራ ነው።

ከተግባራቱ መካከል አገልግሎት አሰጣጡን በቴክኖሎጂ መደገፍ አንዱ መሆኑን አንስተው፤ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰዋል።

በዚህም ካሁን ቀደም በዘርፉ የነበሩ ተግዳሮቶች እየተሻሻሉ መምጣታቸውን ጠቁመዋል፡፡

የኤሌክትሪክ መቆራረጥን ለማስቀረት የተጀመረው ቴክኖሎጂን መሰረት ያደረገ አሰራር ማህበረሰቡ እንዲያውቀው ለማድረግና ብልሹ አሰራሮችን ለማጋለጥ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ሚና የላቀ ነው ብለዋል።

የአገልግሎቱ የኮሙኒኬሽን ዘርፍ ስራ አስፈፃሚ አንዋር አብራር በበኩላቸው፤ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማትን ከስርቆት ለመጠበቅ የማህበረሰቡ ተሳትፎ እንደሚያስፈልግ አንስተዋል።

መገናኛ ብዙሃንም በማህበረሰቡ ዘንድ ግንዛቤ ከመፍጠር አኳያ የበኩላቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ነው የተናገሩት፡፡

ለዚህም አገልግሎቱ ከመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ጋር ተቀራርቦ መስራት የሚያስችለውን ጉብኝት ማድረግና የሚድያ ፎረም ማቋቋም ማስፈለጉን ጠቅሰዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025