
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 14/2017(ኢዜአ)፦የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርሙ ኢንተርፕራይዞች ከሀገር ባለፈ በዓለም ደረጃም የተሻለ እንዲንቀሳቀሱ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ገለጹ።
ርዕሰ-መስተዳድሩ በብዝሃ የኢኮኖሚ ዘርፎች የሥራ ዕድል የተፈጠረላቸው ኢንተርፕራይዞች የተሻለ እድገት እያስመዘገቡ መሆናቸውንም ጠቁመዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሥራ ዕድል ፈጠራ ምክር ቤት የ2017 በጀት ዓመት ጉባኤ በአርባምንጭ ከተማ የተካሔደ ሲሆን በተለያዩ የዕድገት ተኮር ዘርፎች ውጤታማ ለሆኑ ኢንተርፕራይዞችም እውቅና ተሰጥቷቸዋል።

የክልሉ ርዕሰ-መስተዳድር በወቅቱ እንደተናገሩት ኢንተርፕራይዞች በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም በመታገዝ የውስጥ ፀጋዎችን ተጠቅመው ተኪ ምርቶችን በማምረት ራሳቸውን ከመቻል ባለፈ የክልሉ ኢኮኖሚ እንዲያንሰራራ የበኩላቸውን ሚና እየተወጡ ይገኛሉ።
የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርሙ ኢንተርፕራይዞች ከሀገር ባለፈ በዓለም ደረጃ በኢኮኖሚ የበለጸጉ እንዲሆኑ ምቹ ምህዳር እየፈጠረ መሆኑንም አንስተዋል።
ልፋትን ወደ ውጤት ፣ፀጋን ወደ ሀብት በመቀየር ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ ኢንተርፕራይዞቹ ጠንክረው ሊሠሩ እንደሚገባ ጠቅሰው ፤ ለዚህም አመራሮች፣ ቤተሰብ ፣የፋይናንስና የትምህርት ተቋማት መደገፍ እንዳለባቸው አሳስበዋል።
የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ሃላፊ አበባየሁ ታደሰ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በክልሉ በርካታ ኢንተርፕራይዞች በሌማት ትሩፋትና በሌሎች መስኮች ተኪና ወጪ ምርቶችን በማምረት ዕድገትን ለማፋጠን ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከቱ እንደሚገኙ ተናግረዋል።

መንግስት ለኢንተርፕራይዞች ለውጥ ብድር ፣የመስሪያና መሸጫ ስፍራዎችን በማመቻቸት እንዲሁም ክህሎት መር ስልጠና በመስጠት የበኩሉን እየተወጣ ይገኛል ብለዋል።
ከክልሉ ኢንተርፕራይዞች መካከል ከጌዴኦ ዞን ይርጋ ጨፌ ወረዳ የ"ዘፍጥረት" ቡና ችግኝ ማህበር ሰብሳቢ ወጣት ታሪኩ ሎሌ በሰጠው አስተያየት፤ ተደራጅተው የቡና ችግኝ በማፍላት ለአርሶ አደሮችና ባለሀብቶች በመሸጥ ገቢ እያገኙ መሆናቸውን ገልጿል።
መንግስት ባመቻቸላቸው 50 ሺህ ብር ብድር በመታገዝ በሁለት ዓመታት ውስጥ ካፒታላቸውን አምስት ሚሊዮን ብር ማድረስ እንደቻሉ አስረድቷል።

በመድረኩ በተለያዩ የዕድገት ተኮር ዘርፎች ውጤታማ የሆኑ ኢንተርፕራይዞች እውቅና የተሰጣቸው ሲሆን፤ ምርቶቻቸውን የሚያሳይ የፎቶ አውደ-ርዕይ ቀርቦ ተጎብኝቷል።
ለአንድ ቀን በተዘጋጀው መድረክ ላይ የክልልና የዞን አመራር አካላት ፣በክልሉ ግንባር ቀደም የሆኑ ኢንተርፕራይዞችና የፋይናንስ ተቋማት ተሳተፈዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026