የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርሙ ኢንተርፕራይዞችን የተሻለ ውጤታማ እያደረጋቸው ነው -ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ

Jun 23, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 14/2017(ኢዜአ)፦የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርሙ ኢንተርፕራይዞች ከሀገር ባለፈ በዓለም ደረጃም የተሻለ እንዲንቀሳቀሱ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ገለጹ።

ርዕሰ-መስተዳድሩ በብዝሃ የኢኮኖሚ ዘርፎች የሥራ ዕድል የተፈጠረላቸው ኢንተርፕራይዞች የተሻለ እድገት እያስመዘገቡ መሆናቸውንም ጠቁመዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሥራ ዕድል ፈጠራ ምክር ቤት የ2017 በጀት ዓመት ጉባኤ በአርባምንጭ ከተማ የተካሔደ ሲሆን በተለያዩ የዕድገት ተኮር ዘርፎች ውጤታማ ለሆኑ ኢንተርፕራይዞችም እውቅና ተሰጥቷቸዋል።

የክልሉ ርዕሰ-መስተዳድር በወቅቱ እንደተናገሩት ኢንተርፕራይዞች በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም በመታገዝ የውስጥ ፀጋዎችን ተጠቅመው ተኪ ምርቶችን በማምረት ራሳቸውን ከመቻል ባለፈ የክልሉ ኢኮኖሚ እንዲያንሰራራ የበኩላቸውን ሚና እየተወጡ ይገኛሉ።

የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርሙ ኢንተርፕራይዞች ከሀገር ባለፈ በዓለም ደረጃ በኢኮኖሚ የበለጸጉ እንዲሆኑ ምቹ ምህዳር እየፈጠረ መሆኑንም አንስተዋል።

ልፋትን ወደ ውጤት ፣ፀጋን ወደ ሀብት በመቀየር ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ ኢንተርፕራይዞቹ ጠንክረው ሊሠሩ እንደሚገባ ጠቅሰው ፤ ለዚህም አመራሮች፣ ቤተሰብ ፣የፋይናንስና የትምህርት ተቋማት መደገፍ እንዳለባቸው አሳስበዋል።

የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ሃላፊ አበባየሁ ታደሰ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በክልሉ በርካታ ኢንተርፕራይዞች በሌማት ትሩፋትና በሌሎች መስኮች ተኪና ወጪ ምርቶችን በማምረት ዕድገትን ለማፋጠን ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከቱ እንደሚገኙ ተናግረዋል።

መንግስት ለኢንተርፕራይዞች ለውጥ ብድር ፣የመስሪያና መሸጫ ስፍራዎችን በማመቻቸት እንዲሁም ክህሎት መር ስልጠና በመስጠት የበኩሉን እየተወጣ ይገኛል ብለዋል።

ከክልሉ ኢንተርፕራይዞች መካከል ከጌዴኦ ዞን ይርጋ ጨፌ ወረዳ የ"ዘፍጥረት" ቡና ችግኝ ማህበር ሰብሳቢ ወጣት ታሪኩ ሎሌ በሰጠው አስተያየት፤ ተደራጅተው የቡና ችግኝ በማፍላት ለአርሶ አደሮችና ባለሀብቶች በመሸጥ ገቢ እያገኙ መሆናቸውን ገልጿል።

መንግስት ባመቻቸላቸው 50 ሺህ ብር ብድር በመታገዝ በሁለት ዓመታት ውስጥ ካፒታላቸውን አምስት ሚሊዮን ብር ማድረስ እንደቻሉ አስረድቷል።

በመድረኩ በተለያዩ የዕድገት ተኮር ዘርፎች ውጤታማ የሆኑ ኢንተርፕራይዞች እውቅና የተሰጣቸው ሲሆን፤ ምርቶቻቸውን የሚያሳይ የፎቶ አውደ-ርዕይ ቀርቦ ተጎብኝቷል።

ለአንድ ቀን በተዘጋጀው መድረክ ላይ የክልልና የዞን አመራር አካላት ፣በክልሉ ግንባር ቀደም የሆኑ ኢንተርፕራይዞችና የፋይናንስ ተቋማት ተሳተፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የአፍሪካ የልማትና ትብብር ዓርማ - ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በታዋቂው ታይም መጽሔት ገጽ

አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...

Sep 14, 2026

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026