
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 14/2017(ኢዜአ)፦የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርሙ ኢንተርፕራይዞች ከሀገር ባለፈ በዓለም ደረጃም የተሻለ እንዲንቀሳቀሱ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ገለጹ።
ርዕሰ-መስተዳድሩ በብዝሃ የኢኮኖሚ ዘርፎች የሥራ ዕድል የተፈጠረላቸው ኢንተርፕራይዞች የተሻለ እድገት እያስመዘገቡ መሆናቸውንም ጠቁመዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሥራ ዕድል ፈጠራ ምክር ቤት የ2017 በጀት ዓመት ጉባኤ በአርባምንጭ ከተማ የተካሔደ ሲሆን በተለያዩ የዕድገት ተኮር ዘርፎች ውጤታማ ለሆኑ ኢንተርፕራይዞችም እውቅና ተሰጥቷቸዋል።

የክልሉ ርዕሰ-መስተዳድር በወቅቱ እንደተናገሩት ኢንተርፕራይዞች በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም በመታገዝ የውስጥ ፀጋዎችን ተጠቅመው ተኪ ምርቶችን በማምረት ራሳቸውን ከመቻል ባለፈ የክልሉ ኢኮኖሚ እንዲያንሰራራ የበኩላቸውን ሚና እየተወጡ ይገኛሉ።
የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርሙ ኢንተርፕራይዞች ከሀገር ባለፈ በዓለም ደረጃ በኢኮኖሚ የበለጸጉ እንዲሆኑ ምቹ ምህዳር እየፈጠረ መሆኑንም አንስተዋል።
ልፋትን ወደ ውጤት ፣ፀጋን ወደ ሀብት በመቀየር ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ ኢንተርፕራይዞቹ ጠንክረው ሊሠሩ እንደሚገባ ጠቅሰው ፤ ለዚህም አመራሮች፣ ቤተሰብ ፣የፋይናንስና የትምህርት ተቋማት መደገፍ እንዳለባቸው አሳስበዋል።
የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ሃላፊ አበባየሁ ታደሰ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በክልሉ በርካታ ኢንተርፕራይዞች በሌማት ትሩፋትና በሌሎች መስኮች ተኪና ወጪ ምርቶችን በማምረት ዕድገትን ለማፋጠን ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከቱ እንደሚገኙ ተናግረዋል።

መንግስት ለኢንተርፕራይዞች ለውጥ ብድር ፣የመስሪያና መሸጫ ስፍራዎችን በማመቻቸት እንዲሁም ክህሎት መር ስልጠና በመስጠት የበኩሉን እየተወጣ ይገኛል ብለዋል።
ከክልሉ ኢንተርፕራይዞች መካከል ከጌዴኦ ዞን ይርጋ ጨፌ ወረዳ የ"ዘፍጥረት" ቡና ችግኝ ማህበር ሰብሳቢ ወጣት ታሪኩ ሎሌ በሰጠው አስተያየት፤ ተደራጅተው የቡና ችግኝ በማፍላት ለአርሶ አደሮችና ባለሀብቶች በመሸጥ ገቢ እያገኙ መሆናቸውን ገልጿል።
መንግስት ባመቻቸላቸው 50 ሺህ ብር ብድር በመታገዝ በሁለት ዓመታት ውስጥ ካፒታላቸውን አምስት ሚሊዮን ብር ማድረስ እንደቻሉ አስረድቷል።

በመድረኩ በተለያዩ የዕድገት ተኮር ዘርፎች ውጤታማ የሆኑ ኢንተርፕራይዞች እውቅና የተሰጣቸው ሲሆን፤ ምርቶቻቸውን የሚያሳይ የፎቶ አውደ-ርዕይ ቀርቦ ተጎብኝቷል።
ለአንድ ቀን በተዘጋጀው መድረክ ላይ የክልልና የዞን አመራር አካላት ፣በክልሉ ግንባር ቀደም የሆኑ ኢንተርፕራይዞችና የፋይናንስ ተቋማት ተሳተፈዋል።
አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...
Sep 14, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026