የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የሃላላ ኬላ ሎጅ ተደብቆ የነበረውን የቀደምት አባቶች ታሪክ በመግለጥ ለቱሪዝም ኢንቨስትመንት ፍሰት ከፍተኛ አቅም ፈጥሯል

Jun 24, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሰኔ 16/2017 (ኢዜአ)፦የሃላላ ኬላ ሎጅ ተደብቆ የነበረውን የቀደምት አባቶች ታሪክ በመግለጥ ለአካባቢው ማህበረሰብ የቱሪዝም ኢንቨስትመንት ፍሰት ከፍተኛ አቅም መፍጠሩን የዳውሮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳዊት ገበየሁ ገለጹ።

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት በገበታ ለሀገር የኮይሻ ፕሮጀክት አካል የሆነው የሃላላ ኬላ ሎጅ በሚያዚያ 2015 ዓ.ም ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት መደረጉ ይታወሳል።

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ዳውሮ ዞን ግልገል ጊቤ-3 የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድብን ተንተርሶ የተገነባው የሃላላ ኬላ ሎጅም በቱሪስት መዳረሻነት የሚያገለግል ድንቅ የመስህብ ስፍራ ሆኗል።

የሃላላ ኬላ ሎጅ ወደ ስፍራው ለሚያቀኑ ቱሪስቶች ታሪክ፣ተፈጥሮና ዘመናዊ የግንባታ ጥበብ ተሰናስለው ውብ ገጽታን በፈጠሩበት አስደናቂ የዓለም አቀፍ የመዳረሻ የተሻለ ጊዜ የሚያሳልፉበትን ዕድል ተፈጥሯል።


ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የዳውሮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳዊት ገበየሁ÷ ሃላላ ኬላ ቀደምት አባቶች ከ300 ዓመታት በፊት 1 ሺህ 225 ኪሎ ሜትር የሚረዝም ባለ ሰባት ረድፍ ያለው የድንጋይ ግንብ የገነቡበት ታሪካዊ ስፍራ ነው ብለዋል።

በዚህ መነሻነትም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሃሳብ አመንጪነት የቀደምት አባቶችን የታሪክ አሻራ በሚገባው ልክ ማስታወስ የሚስያችል የሃላላ ኬላ ሎጅ ኢኮ-ቱሪዝም እንዲገነባ ማድረጋቸውን ገልጸዋል።


የሃላላ ኬላ ሎጅ የዳውሮን ህዝብ ታሪክና ልማት በማስተዋወቅ በሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ገጽታ ግንባታ ጉልህ ፋይዳ እያበረከተ መሆኑን ተናግረዋል።

የለውጡ መንግስት ለአካባቢ ማህበረሰብ የፈጠረው የልማት ዕድልም የቱሪዝም አገልግሎት ዘርፍ ኢንቨስትመንት ፍሰትን በማሳደግ ከፍተኛ የገቢ ምንጭ እየተፈጠረ እንደሚገኝ አንስተዋል።

የሃላላ ኬላ ሎጅ የግልገል ጊቤ-3 የኤልክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድብን ተንተርሶ መገንባቱም ወጣቶች በጀልባ መዝናኛና ሌሎች የስራ ዕድል መስኮች ተጠቃሚ መሆናቸውን አስረድተዋል።


የሃላላ ኬላ ሎጅ ኢኮ-ቱሪዝም መገንባቱም የዳውሮን ህዝብ ባህላዊ የአመጋገብና የአኗኗር ሥርዓት በማስተዋወቅ በገጽታ ግንባታ አይነተኛ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ አስረድተዋል።

ከዚህ በተጨማሪም የሎጁ መገንባት ተደብቆ የቆየውን የቀደምት አባቶች የታሪክ አሻራ በመግለጥ በቱሪስት ፍሰት የማህበረሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን ገልጸዋል።

የዳውሮ ዞን ከሃላላ ኬላ ኢኮ ቱሪዝም በተጨማሪ በዳውሮና ኮንታ ዞኖች መካከል የሚገኘው የጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፓርክን ጨምሮ ለቱሪዝም ልማት አቅም የሚሆኑ ጸጋዎች መኖራቸውን አንስተዋል።

በዚህም በዳውሮ ዞን መዋዕለነዋያቸውን ፈሰስ የማድረግ ፍላጎት ያላቸው አልሚ ባለሃብቶች በግብርና፣በሆቴልና ቱሪዝም አገልግሎት ዘርፍ መሰማራት የሚችሉበት ሰፊ ዕድል መኖሩን መልዕክት አስተላልፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026