የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የሃላላ ኬላ ሎጅ ተደብቆ የነበረውን የቀደምት አባቶች ታሪክ በመግለጥ ለቱሪዝም ኢንቨስትመንት ፍሰት ከፍተኛ አቅም ፈጥሯል

Jun 24, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሰኔ 16/2017 (ኢዜአ)፦የሃላላ ኬላ ሎጅ ተደብቆ የነበረውን የቀደምት አባቶች ታሪክ በመግለጥ ለአካባቢው ማህበረሰብ የቱሪዝም ኢንቨስትመንት ፍሰት ከፍተኛ አቅም መፍጠሩን የዳውሮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳዊት ገበየሁ ገለጹ።

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት በገበታ ለሀገር የኮይሻ ፕሮጀክት አካል የሆነው የሃላላ ኬላ ሎጅ በሚያዚያ 2015 ዓ.ም ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት መደረጉ ይታወሳል።

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ዳውሮ ዞን ግልገል ጊቤ-3 የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድብን ተንተርሶ የተገነባው የሃላላ ኬላ ሎጅም በቱሪስት መዳረሻነት የሚያገለግል ድንቅ የመስህብ ስፍራ ሆኗል።

የሃላላ ኬላ ሎጅ ወደ ስፍራው ለሚያቀኑ ቱሪስቶች ታሪክ፣ተፈጥሮና ዘመናዊ የግንባታ ጥበብ ተሰናስለው ውብ ገጽታን በፈጠሩበት አስደናቂ የዓለም አቀፍ የመዳረሻ የተሻለ ጊዜ የሚያሳልፉበትን ዕድል ተፈጥሯል።


ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የዳውሮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳዊት ገበየሁ÷ ሃላላ ኬላ ቀደምት አባቶች ከ300 ዓመታት በፊት 1 ሺህ 225 ኪሎ ሜትር የሚረዝም ባለ ሰባት ረድፍ ያለው የድንጋይ ግንብ የገነቡበት ታሪካዊ ስፍራ ነው ብለዋል።

በዚህ መነሻነትም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሃሳብ አመንጪነት የቀደምት አባቶችን የታሪክ አሻራ በሚገባው ልክ ማስታወስ የሚስያችል የሃላላ ኬላ ሎጅ ኢኮ-ቱሪዝም እንዲገነባ ማድረጋቸውን ገልጸዋል።


የሃላላ ኬላ ሎጅ የዳውሮን ህዝብ ታሪክና ልማት በማስተዋወቅ በሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ገጽታ ግንባታ ጉልህ ፋይዳ እያበረከተ መሆኑን ተናግረዋል።

የለውጡ መንግስት ለአካባቢ ማህበረሰብ የፈጠረው የልማት ዕድልም የቱሪዝም አገልግሎት ዘርፍ ኢንቨስትመንት ፍሰትን በማሳደግ ከፍተኛ የገቢ ምንጭ እየተፈጠረ እንደሚገኝ አንስተዋል።

የሃላላ ኬላ ሎጅ የግልገል ጊቤ-3 የኤልክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድብን ተንተርሶ መገንባቱም ወጣቶች በጀልባ መዝናኛና ሌሎች የስራ ዕድል መስኮች ተጠቃሚ መሆናቸውን አስረድተዋል።


የሃላላ ኬላ ሎጅ ኢኮ-ቱሪዝም መገንባቱም የዳውሮን ህዝብ ባህላዊ የአመጋገብና የአኗኗር ሥርዓት በማስተዋወቅ በገጽታ ግንባታ አይነተኛ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ አስረድተዋል።

ከዚህ በተጨማሪም የሎጁ መገንባት ተደብቆ የቆየውን የቀደምት አባቶች የታሪክ አሻራ በመግለጥ በቱሪስት ፍሰት የማህበረሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን ገልጸዋል።

የዳውሮ ዞን ከሃላላ ኬላ ኢኮ ቱሪዝም በተጨማሪ በዳውሮና ኮንታ ዞኖች መካከል የሚገኘው የጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፓርክን ጨምሮ ለቱሪዝም ልማት አቅም የሚሆኑ ጸጋዎች መኖራቸውን አንስተዋል።

በዚህም በዳውሮ ዞን መዋዕለነዋያቸውን ፈሰስ የማድረግ ፍላጎት ያላቸው አልሚ ባለሃብቶች በግብርና፣በሆቴልና ቱሪዝም አገልግሎት ዘርፍ መሰማራት የሚችሉበት ሰፊ ዕድል መኖሩን መልዕክት አስተላልፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የአፍሪካ የልማትና ትብብር ዓርማ - ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በታዋቂው ታይም መጽሔት ገጽ

አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...

Sep 14, 2026

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026