የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

አሜሪካ ኢንቨስትመንቷን በአፍሪካ እንድታስፋፋ የአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት አኪንዉሚ አዴሲና(ዶ/ር) ጥሪ አቀረቡ

Jun 25, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 17/2017(ኢዜአ)፦አሜሪካ የኢንቨስትመንት ተሳትፎዋን በአፍሪካ እንድታስፋፋ የአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት አኪንዉሚ አዴሲና(ዶ/ር) ጠየቁ ።

የአፍሪካና የአሜሪካ የቢዝነስ ጉባኤ በአንጎላ ርዕሰ መዲና ሉዋንዳ እየተካሔደ ይገኛል።

በጉባኤው ላይ ፕሬዝዳንቱ አሜሪካ ካላት ከፍተኛ የካፒታል አቅም አኳያ በአፍሪካ የኢንቨስትመንት ተሳትፎዋን እንድታሰፋና ከአፍሪካ ጋር ያላትን ስትራቴጂካዊ የትብብር አድማስ እንድታጠናክር ጠይቀዋል።

የትኛውም ብልህ ባለሃብት አሁን ኢንቨስትመንትን ሲያስብ አፍሪካን ማሰብ አለበት ያሉት ፕሬዝዳንቱ ለዚህም አፍሪካ ምቹ የኢንቨስትመንት መዳረሻ ስለሆነች መሆኗን አሃዛዊ መረጃ ጠቅሰው አስረድተዋል።

ዓለም ላይ ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት እያስመዘገቡ ከሚገኙ አገራት መካከል ቁጥራቸው ቀላል የማይባል የአፍሪካ አገራት መኖራቸውን አንስተዋል።

ሰፊ ያልታረሰ መሬት እና የሃይል ሽግግር እውን ማድረግ የሚያስችሉ ማዕድናት መኖራቸው አህጉሪቱን ተፈላጊ ያደርጋታል ብለዋል።

በመድረኩ እኔን ሳይሆን መረጃውን እመኑ በማለት የሞገቱት የባንኩ ፕሬዝዳንት አሁን ላይ የመንግሥታቱን መረጃ በመጥቀስ አፍሪካ ውስጥ ኢንቨስት ማድረግ ከ15 በመቶ እስከ 20 በመቶ የወጪ ተመላሽ ትርፍ የሚያስገኝ መሆኑን አስረድተዋል።

በጉባኤው ላይም ፕሬዝዳንቱ በአፍሪካ በኢኮኖሚ መስክ ላበረከቱት የአመራርነት ሚና እውቅና ተሰጧቸዋል።

እውቅናው የባንኩ ፕሬዝዳንት አኪንዉሚ አዴሲና(ዶ/ር) ላለፉት 10 ዓመታት የመሩት አህጉራዊ የፖሊሲ ባንክ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች የኑሮ ሁኔታ እንዲሻሻልና የአህጉሪቷ ልማት እንዲፋጠን ያበረከቱትን የአመራርነት ሚና ከግምት ያስገባ መሆኑም ተጠቅሷል።

በጉባኤው ላይ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴን ጨምሮ የተለያዩ የአፍሪካ አገራት መሪዎች፣ሚኒስትሮች፣ የመንግሥታት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም የአሜሪካ መንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናት፣የሁለቱም ወገን የቢዝነስ መሪዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026