
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 17/2017(ኢዜአ)፦አሜሪካ የኢንቨስትመንት ተሳትፎዋን በአፍሪካ እንድታስፋፋ የአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት አኪንዉሚ አዴሲና(ዶ/ር) ጠየቁ ።
የአፍሪካና የአሜሪካ የቢዝነስ ጉባኤ በአንጎላ ርዕሰ መዲና ሉዋንዳ እየተካሔደ ይገኛል።
በጉባኤው ላይ ፕሬዝዳንቱ አሜሪካ ካላት ከፍተኛ የካፒታል አቅም አኳያ በአፍሪካ የኢንቨስትመንት ተሳትፎዋን እንድታሰፋና ከአፍሪካ ጋር ያላትን ስትራቴጂካዊ የትብብር አድማስ እንድታጠናክር ጠይቀዋል።
የትኛውም ብልህ ባለሃብት አሁን ኢንቨስትመንትን ሲያስብ አፍሪካን ማሰብ አለበት ያሉት ፕሬዝዳንቱ ለዚህም አፍሪካ ምቹ የኢንቨስትመንት መዳረሻ ስለሆነች መሆኗን አሃዛዊ መረጃ ጠቅሰው አስረድተዋል።
ዓለም ላይ ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት እያስመዘገቡ ከሚገኙ አገራት መካከል ቁጥራቸው ቀላል የማይባል የአፍሪካ አገራት መኖራቸውን አንስተዋል።
ሰፊ ያልታረሰ መሬት እና የሃይል ሽግግር እውን ማድረግ የሚያስችሉ ማዕድናት መኖራቸው አህጉሪቱን ተፈላጊ ያደርጋታል ብለዋል።
በመድረኩ እኔን ሳይሆን መረጃውን እመኑ በማለት የሞገቱት የባንኩ ፕሬዝዳንት አሁን ላይ የመንግሥታቱን መረጃ በመጥቀስ አፍሪካ ውስጥ ኢንቨስት ማድረግ ከ15 በመቶ እስከ 20 በመቶ የወጪ ተመላሽ ትርፍ የሚያስገኝ መሆኑን አስረድተዋል።
በጉባኤው ላይም ፕሬዝዳንቱ በአፍሪካ በኢኮኖሚ መስክ ላበረከቱት የአመራርነት ሚና እውቅና ተሰጧቸዋል።
እውቅናው የባንኩ ፕሬዝዳንት አኪንዉሚ አዴሲና(ዶ/ር) ላለፉት 10 ዓመታት የመሩት አህጉራዊ የፖሊሲ ባንክ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች የኑሮ ሁኔታ እንዲሻሻልና የአህጉሪቷ ልማት እንዲፋጠን ያበረከቱትን የአመራርነት ሚና ከግምት ያስገባ መሆኑም ተጠቅሷል።
በጉባኤው ላይ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴን ጨምሮ የተለያዩ የአፍሪካ አገራት መሪዎች፣ሚኒስትሮች፣ የመንግሥታት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም የአሜሪካ መንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናት፣የሁለቱም ወገን የቢዝነስ መሪዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026