
ገንዳ ውሀ፤ ሰኔ 19/2017(ኢዜአ)፦ በምዕራብ ጎንደር ዞን የግብርና ምርትና ምርታማነትን ይበልጥ ለማሳደግ ለዘመናዊ አስተራረስና ግብዓት አቅርቦት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።
በመምሪያው የሰብል ልማት ቡድን መሪ ጌትነት ካሳሁን፤ ዞኑ ገበያ ተኮር ምርቶችን በስፋት ማምረት የሚያስችል የእርሻ መሬት መገኛ መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህም በ2017/2018 የምርት ዘመን 530ሺህ ሄክታር የሚጠጋ መሬት በዘመናዊ መንገድ አርሶ አደሩንና ባለሃብቱን በማሳተፍ ለማልማት ታቅዶ ወደ ተግባር መገባቱን ገልጸዋል።
የሚመረተውም አኩሪ አተር፣ ሰሊጥ፣ ማሽላ፣ ጥጥ፣ ማሾ፣ ሱፍና ሌሎች ገበያ ተኮር ሰብሎች መሆናቸውን ተናግረዋል።

የግብርናውን ምርታማነት ይበልጥ ለማሳደግ ከ530 በላይ ትራክተሮችና በቂ ግብዓት መቅረቡን አመልክተው፤ ከዚህም 12 ነጥብ 6 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱን ጠቁመዋል።
በዘር ከሚሸፈነው ውሰጥ 434ሺህ ሄክታሩ በአርሶ አደሮች፤ ቀሪው በባለሃብቶች መሆኑን ተናግረዋል።
ከመተማ ወረዳ አርሶ አደር ዮሐንስ ስዩም በሰጡት አስተያየት፤ በዚህ የምርት ዘመን 10 ሄክታር መሬታቸውን የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ማዳበሪያን በመጠቀም በዘር የመሸፈን ስራ እያከናወኑ እንደሚገኙ ገልጸዋል።
ሰሊጥ፣ አኩሪ አተር፣ ማሽላና ጤፍ የሚያለሟቸው የሰብል ዓይነቶች መሆናቸውን ጠቅሰዋል።
በግብርና ኢንቨስትመንት የተሰማሩት አቶ ቃሲም አህመድ በበኩላቸው፤ 50 ሄክታር መሬታቸውን እስከ ሀምሌ አጋማሽ ድረስ በሰሊጥ፣ አኩሪ አተር፣ ጥጥና ማሽላ ለማልማት ከወዲሁ ወደ ስራ መግባታቸውን ገልጸዋል።
ከግብርና መምሪያው የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው፤ በዞኑ ባለፈው የምርት ዘመን 521ሺህ ሄክታር የሚጠጋ መሬት ታርሶ ከ8 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ተገኝቷል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026