የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በዞኑ ምርታማነትን ይበልጥ ለማሳደግ ለዘመናዊ አስተራረስ ትኩረት ተሰጥቶ ተግባራዊ እየተደረገ ነው

Jun 27, 2025

IDOPRESS

ገንዳ ውሀ፤ ሰኔ 19/2017(ኢዜአ)፦ በምዕራብ ጎንደር ዞን የግብርና ምርትና ምርታማነትን ይበልጥ ለማሳደግ ለዘመናዊ አስተራረስና ግብዓት አቅርቦት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።

በመምሪያው የሰብል ልማት ቡድን መሪ ጌትነት ካሳሁን፤ ዞኑ ገበያ ተኮር ምርቶችን በስፋት ማምረት የሚያስችል የእርሻ መሬት መገኛ መሆኑን ተናግረዋል።

በዚህም በ2017/2018 የምርት ዘመን 530ሺህ ሄክታር የሚጠጋ መሬት በዘመናዊ መንገድ አርሶ አደሩንና ባለሃብቱን በማሳተፍ ለማልማት ታቅዶ ወደ ተግባር መገባቱን ገልጸዋል።

የሚመረተውም አኩሪ አተር፣ ሰሊጥ፣ ማሽላ፣ ጥጥ፣ ማሾ፣ ሱፍና ሌሎች ገበያ ተኮር ሰብሎች መሆናቸውን ተናግረዋል።


የግብርናውን ምርታማነት ይበልጥ ለማሳደግ ከ530 በላይ ትራክተሮችና በቂ ግብዓት መቅረቡን አመልክተው፤ ከዚህም 12 ነጥብ 6 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱን ጠቁመዋል።

በዘር ከሚሸፈነው ውሰጥ 434ሺህ ሄክታሩ በአርሶ አደሮች፤ ቀሪው በባለሃብቶች መሆኑን ተናግረዋል።

ከመተማ ወረዳ አርሶ አደር ዮሐንስ ስዩም በሰጡት አስተያየት፤ በዚህ የምርት ዘመን 10 ሄክታር መሬታቸውን የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ማዳበሪያን በመጠቀም በዘር የመሸፈን ስራ እያከናወኑ እንደሚገኙ ገልጸዋል።

ሰሊጥ፣ አኩሪ አተር፣ ማሽላና ጤፍ የሚያለሟቸው የሰብል ዓይነቶች መሆናቸውን ጠቅሰዋል።

በግብርና ኢንቨስትመንት የተሰማሩት አቶ ቃሲም አህመድ በበኩላቸው፤ 50 ሄክታር መሬታቸውን እስከ ሀምሌ አጋማሽ ድረስ በሰሊጥ፣ አኩሪ አተር፣ ጥጥና ማሽላ ለማልማት ከወዲሁ ወደ ስራ መግባታቸውን ገልጸዋል።

ከግብርና መምሪያው የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው፤ በዞኑ ባለፈው የምርት ዘመን 521ሺህ ሄክታር የሚጠጋ መሬት ታርሶ ከ8 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ተገኝቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026