የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ኢትዮጵያ በክህሎት ልማት ዘርፍ ቀጣናዊ ትስስርን እና የጋራ ተጠቃሚነትን እያረጋገጠች ነው

Jun 27, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ ፤ ሰኔ 19/2017 (ኢዜአ ) ኢትዮጵያ በክህሎት ልማት ዘርፍ ቀጣናዊ ትስስርን እና የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ ተግባራትን አጠናክራ መቀጠሏን የሥራ እና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት፥ የክህሎት ልማት ዲፕሎማሲ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ።

ባለፉት ዓመታት በፌደራል ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ቀጠናዊ ትስስርን ለማጠናከር የሚያስችሉ ነጻ የትምህርት እድሎች ለደቡብ ሱዳን፣ ሶማሊያና ሌሎችም የጎረቤት ሀገራት ዜጎች እየሰጠን ነው ብለዋል፡፡


ነጻ የትምህርት እድሎች የክህሎት ሰልጣኞቹ ወደ ሀገራቸው ከተመለሱ በኋላ የኢትዮጵያን ባህልና ገጽታ በማስተዋወቅ አምባሳደር እንዲሆኑ ከፍተኛ ሚና እንዳላቸው አንስተዋል፡፡

በምስራቅ አፍሪካ ቀጠናዊ የሆነ የስልጠና ማዕቀፍ በማዘጋጀት የእርስ በእርስ የክህሎት ልማት የስልጠና ዕድሎች እየተፈጠሩ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡

በሀገራቱ መካከል በክህሎት ዘርፍ የልምድ ልውውጥ እየተደረገ መሆኑን ያነሱት ሚኒስትር ዴኤታው የምስራቅ አፍሪካ አገራት ባለሙያዎች ወደ ኢትዮጵያ መጥተው ልምድ መውሰዳቸውን በአብነት ጠቅሰዋል፡፡


ባለፉት ዓመታት በዘርፉ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ቀጠናዊ ትስስር ለመፍጠር ከማገዛቸው ባለፈ በዲፕሎማሲው ላይ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑን ነው የጠቀሱት።

በኢትዮጵያ ቅድሚያ ለጎረቤት ሀገራት በሚለው የውጭ ግንኙነት ፖሊሲዋ በክህሎት ዘርፍ የሚኖረውን ቀጠናዊ ትስስር ለማስፋት የሚያስችሉ ስራዎች እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል፡፡

የፌደራል ቴክኒክና ሙያ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር(ዶ/ር) በበኩላቸው ባለፉት አምስት ዓመታት በየዓመቱ 250 ለሚደርሱ የጎረቤት ሀገራት ዜጎች በተለያዩ የሙያ ዘርፎች የትምህርት ዕድል መሰጠቱን ጠቁመዋል፡፡


ተመርቀው ወደ ሀገራቸው የተመለሱ ተማሪዎች በሀገራቸው አሰልጣኞች፣ ዲኖች እንዲሁም የተለያዩ የስልጠና ተቋማት አመራሮችና ፖሊሲ አውጪዎች ሆነው በመስራት ላይ እንደሚገኙም አንስተዋል።

ከደቡብ ሱዳን የመጣው ተማሪ ጋሪማ ቤልቸር በኢንስቲትዩቱ እውቀትና ክህሎት ከማግኘት በተጨማሪ በትምህርቱ ውጤታማ እንዲሆን ከፍተኛ ድጋፍ እየተደረገለት እንደሚገኝ ተናግሯል።


በትምህርት ቆይታውም በርካታ ኢትዮጵያውያን ጓደኞች ማፍራቱንና እንደ ሁለተኛ ቤቱ እንደሚሰማው ገልጿል።

ትምህርቱን አጠናቆ ወደ ሀገሩ ሲመለስ ስለ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያን መልካምነትና እንግዳ ተቀባይነት እንደሚመሰክር አረጋግጧል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026