
አዲስ አበባ ፤ ሰኔ 19/2017 (ኢዜአ ) ኢትዮጵያ በክህሎት ልማት ዘርፍ ቀጣናዊ ትስስርን እና የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ ተግባራትን አጠናክራ መቀጠሏን የሥራ እና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት፥ የክህሎት ልማት ዲፕሎማሲ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ።
ባለፉት ዓመታት በፌደራል ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ቀጠናዊ ትስስርን ለማጠናከር የሚያስችሉ ነጻ የትምህርት እድሎች ለደቡብ ሱዳን፣ ሶማሊያና ሌሎችም የጎረቤት ሀገራት ዜጎች እየሰጠን ነው ብለዋል፡፡

ነጻ የትምህርት እድሎች የክህሎት ሰልጣኞቹ ወደ ሀገራቸው ከተመለሱ በኋላ የኢትዮጵያን ባህልና ገጽታ በማስተዋወቅ አምባሳደር እንዲሆኑ ከፍተኛ ሚና እንዳላቸው አንስተዋል፡፡
በምስራቅ አፍሪካ ቀጠናዊ የሆነ የስልጠና ማዕቀፍ በማዘጋጀት የእርስ በእርስ የክህሎት ልማት የስልጠና ዕድሎች እየተፈጠሩ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡
በሀገራቱ መካከል በክህሎት ዘርፍ የልምድ ልውውጥ እየተደረገ መሆኑን ያነሱት ሚኒስትር ዴኤታው የምስራቅ አፍሪካ አገራት ባለሙያዎች ወደ ኢትዮጵያ መጥተው ልምድ መውሰዳቸውን በአብነት ጠቅሰዋል፡፡

ባለፉት ዓመታት በዘርፉ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ቀጠናዊ ትስስር ለመፍጠር ከማገዛቸው ባለፈ በዲፕሎማሲው ላይ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑን ነው የጠቀሱት።
በኢትዮጵያ ቅድሚያ ለጎረቤት ሀገራት በሚለው የውጭ ግንኙነት ፖሊሲዋ በክህሎት ዘርፍ የሚኖረውን ቀጠናዊ ትስስር ለማስፋት የሚያስችሉ ስራዎች እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል፡፡
የፌደራል ቴክኒክና ሙያ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር(ዶ/ር) በበኩላቸው ባለፉት አምስት ዓመታት በየዓመቱ 250 ለሚደርሱ የጎረቤት ሀገራት ዜጎች በተለያዩ የሙያ ዘርፎች የትምህርት ዕድል መሰጠቱን ጠቁመዋል፡፡

ተመርቀው ወደ ሀገራቸው የተመለሱ ተማሪዎች በሀገራቸው አሰልጣኞች፣ ዲኖች እንዲሁም የተለያዩ የስልጠና ተቋማት አመራሮችና ፖሊሲ አውጪዎች ሆነው በመስራት ላይ እንደሚገኙም አንስተዋል።
ከደቡብ ሱዳን የመጣው ተማሪ ጋሪማ ቤልቸር በኢንስቲትዩቱ እውቀትና ክህሎት ከማግኘት በተጨማሪ በትምህርቱ ውጤታማ እንዲሆን ከፍተኛ ድጋፍ እየተደረገለት እንደሚገኝ ተናግሯል።

በትምህርት ቆይታውም በርካታ ኢትዮጵያውያን ጓደኞች ማፍራቱንና እንደ ሁለተኛ ቤቱ እንደሚሰማው ገልጿል።
ትምህርቱን አጠናቆ ወደ ሀገሩ ሲመለስ ስለ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያን መልካምነትና እንግዳ ተቀባይነት እንደሚመሰክር አረጋግጧል፡፡
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026