ሀዋሳ ፤ሰኔ 21/2017 (ኢዜአ) ፡-የኤሌክትሪክ አገልግሎት ፈላጊ ደንበኞች በፍጥነት ምላሽ የሚያገኙበት አሰራር ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሲዳማ ሪጅን አስታወቀ።
በኢትዮጵያ ኢሌክትሪክ አገልግሎት የሲዳማ ሪጅን የኤሌክትሪክ አገልግሎት ለማግኘት የሚጠይቁ አዲስ ደንበኞችን በ24 ሰዓት ውስጥ ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል “ኤሌክትሪክ በአንድ ቀን” የተሰኘ አሰራር ተግባራዊ እያደረገ ይገኛል፡፡
በአገልግሎቱ ሁሉንም ሂደት ጨርሰው ለሚመጡ ደንበኞች በአንድ ቀን ቆጣሪ በማስገባት የኤሌክትሪክ ኃይል የሚያገኙበትን ፈጣንና ቀልጣፋ አሰራር ተግባራዊ እያደረገ ነው።
በዚሁ ጉዳይ ላይ ማብራሪያ የሰጡት የሲዳማ ሪጅን ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ አበበ እድሉ፤ አገልግሎቱ የአዲስ ደንበኞችን ጥያቄ በፍጥነት ምላሽ ለመስጠት በተቀናጀ መልኩ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በዚህም መሰረት ባለፉት 11 ወራት ብቻ 11 ሺህ 23 አዲስ ደንበኞችን የኤሌክትሪክ ሃይል ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ጠቁመው በተጠናከረ መልኩ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል።
በሲዳማ ሪጅን ኤሌክትሪክ አገልግሎት የደንበኞች ተሳትፎና ቁልፍ ደንበኞች ኃላፊ ትዝታ አስናቀ፤ በዘመቻ እየተከናወነ ባለው አሰራር በርካቶች ተጠቃሚ ስለመሆናቸው አንስተዋል።
በተቋሙ ስታንዳርድ መሠረት አንድ ደንበኛ በ10 ቀናት ውስጥ ለጠየቀው አገልግሎት ምላሽ በመስጠት ላይ እንገኛለን ያሉት ኃላፊዋ ስኬታማ ስራ መሆኑንም ተናግረዋል።
አገልግሎቱን ካገኙ ደንበኞች መካከል የሀዋሳ ከተማ ነዋሪው አቶ ዜና ደመቀ፤ አሰራሩ እንግልት የሌለውና ሁላችንንም ያስደሰተ ነው ብለዋል።
ከዚህ በፊት ለጥያቄው ምላሽ ለማግኘት የተለያዩ ምክንያቶች እንደነበሩ አንስተው አሁን ላይ ችግሩ ተፈትቶ የተቀላጠፈ አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑን ገልጸዋል።
የብረታ ብረት ባለሙያ የሆነው ወጣት አሸናፊ ተስፋዬ፤ ለጠየቀው አገልግሎት በአንድ ቀን ቆጣሪ አግኝቶ የኃይል ተጠቃሚ በመሆኑ እየሰራ ባለው የብረታ-ብረት ስራ ውጤታማ መሆኑን ተናግሯል።
አገልግሎቱ ባለፉት 11 ወራት የሥነ-ምግባር ጥሰት ታይቶባቸዋል ባላቸው 48 ባለሙያዎቹ ላይ አስተዳደራዊ እርምጃዎችን መውሰዱም ታውቋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025
ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...
Feb 28, 2025
ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...
Feb 24, 2025