የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የኤሌክትሪክ አገልግሎት ፈላጊ ደንበኞች በፍጥነት ምላሽ የሚያገኙበት አሰራር ተግባራዊ እየተደረገ ነው

Jul 1, 2025

IDOPRESS

ሀዋሳ ፤ሰኔ 21/2017 (ኢዜአ) ፡-የኤሌክትሪክ አገልግሎት ፈላጊ ደንበኞች በፍጥነት ምላሽ የሚያገኙበት አሰራር ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሲዳማ ሪጅን አስታወቀ።

በኢትዮጵያ ኢሌክትሪክ አገልግሎት የሲዳማ ሪጅን የኤሌክትሪክ አገልግሎት ለማግኘት የሚጠይቁ አዲስ ደንበኞችን በ24 ሰዓት ውስጥ ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል “ኤሌክትሪክ በአንድ ቀን” የተሰኘ አሰራር ተግባራዊ እያደረገ ይገኛል፡፡

በአገልግሎቱ ሁሉንም ሂደት ጨርሰው ለሚመጡ ደንበኞች በአንድ ቀን ቆጣሪ በማስገባት የኤሌክትሪክ ኃይል የሚያገኙበትን ፈጣንና ቀልጣፋ አሰራር ተግባራዊ እያደረገ ነው።

በዚሁ ጉዳይ ላይ ማብራሪያ የሰጡት የሲዳማ ሪጅን ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ አበበ እድሉ፤ አገልግሎቱ የአዲስ ደንበኞችን ጥያቄ በፍጥነት ምላሽ ለመስጠት በተቀናጀ መልኩ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህም መሰረት ባለፉት 11 ወራት ብቻ 11 ሺህ 23 አዲስ ደንበኞችን የኤሌክትሪክ ሃይል ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ጠቁመው በተጠናከረ መልኩ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል።


በሲዳማ ሪጅን ኤሌክትሪክ አገልግሎት የደንበኞች ተሳትፎና ቁልፍ ደንበኞች ኃላፊ ትዝታ አስናቀ፤ በዘመቻ እየተከናወነ ባለው አሰራር በርካቶች ተጠቃሚ ስለመሆናቸው አንስተዋል።

በተቋሙ ስታንዳርድ መሠረት አንድ ደንበኛ በ10 ቀናት ውስጥ ለጠየቀው አገልግሎት ምላሽ በመስጠት ላይ እንገኛለን ያሉት ኃላፊዋ ስኬታማ ስራ መሆኑንም ተናግረዋል።

አገልግሎቱን ካገኙ ደንበኞች መካከል የሀዋሳ ከተማ ነዋሪው አቶ ዜና ደመቀ፤ አሰራሩ እንግልት የሌለውና ሁላችንንም ያስደሰተ ነው ብለዋል።

ከዚህ በፊት ለጥያቄው ምላሽ ለማግኘት የተለያዩ ምክንያቶች እንደነበሩ አንስተው አሁን ላይ ችግሩ ተፈትቶ የተቀላጠፈ አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑን ገልጸዋል።


የብረታ ብረት ባለሙያ የሆነው ወጣት አሸናፊ ተስፋዬ፤ ለጠየቀው አገልግሎት በአንድ ቀን ቆጣሪ አግኝቶ የኃይል ተጠቃሚ በመሆኑ እየሰራ ባለው የብረታ-ብረት ስራ ውጤታማ መሆኑን ተናግሯል።

አገልግሎቱ ባለፉት 11 ወራት የሥነ-ምግባር ጥሰት ታይቶባቸዋል ባላቸው 48 ባለሙያዎቹ ላይ አስተዳደራዊ እርምጃዎችን መውሰዱም ታውቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢንዱስትሪ ፓርኩ መገንባት መንግሥት ለዘርፉ የሰጠውን ትኩረት በተጨባጭ ያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...

May 20, 2026

የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል 

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...

May 7, 2026

የከተማዋን ባህል፣ ታሪክ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በማልማት ለኢኮኖሚያዊ ጥቅም የማዋል ተግባራት ይጠናከራሉ

ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...

May 7, 2026

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026