
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 25/2017(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን በክረምት ወራት በዘር ከተሸፈነው 135ሺህ ሄክታር መሬት 1 ነጥብ 9 ሚሊዮን ኩንታል ምርት እንደሚጠበቅ የዞኑ አስተዳዳሪ አብዱልሰላም ዋሪዮ ገለጹ።
የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ እና የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በቦረና ዞን የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ይገኛሉ።

በዛሬው ዕለትም በቦረና ዞን ድሬ ወረዳ በክላስተር የለማ ስንዴን ጎብኝተዋል።
የቦረና ዞን ዋና አስተዳዳሪ አብዱልሰላም ዋሪዮ ለከፍተኛ የስራ ሀላፊዎቹ ባደረጉት ገለጻ፤ በዞኑ ከሁለት ወራት በፊት ጀምሮ እስከ ሰኔ መጨረሻ ድረስ የክረምት ወራት የግብርና ልማት እየተከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
በዚህም 135 ሺህ ሄክታር መሬት በተለያዩ የዘር ዓይነቶች መሸፈኑን ገልጸው ከዚህ ውስጥም ከ56 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በክላስተር እየለማ መሆኑንና 5ሺህ ሄክታር በስንዴ ምርት መሸፈኑን ጠቁመዋል።
ስንዴ፣ ቦሎቄ፣ ጤፍ፣ ማሾ እና ሌሎች ሰብሎችን ማልማት መቻሉን በመግለፅ፥ ከዚህም 1 ነጥብ 9 ሚሊዮን ኩንታል ምርት እንደሚጠበቅ ተናግረዋል።
የቦረና ዞን አሁን ላይ በተሻለ ምርታማነት ላይ እንደሚገኝ ጠቅሰው፥ የአርብቶ አደሩ የስራ ባህል እየተቀየረ መሆኑን ጠቁመዋል።
ምርታማነት እንዲያድግም መንግስት የተለያዩ ድጋፎችን እያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።

በልማት ጉብኝቱ ከፕሬዝዳንት ሽመልስ አብዲሳ በተጨማሪ በብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ ከፍያለው ተፈራ እና ሌሎች የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026