
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 25/2017(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን በክረምት ወራት በዘር ከተሸፈነው 135ሺህ ሄክታር መሬት 1 ነጥብ 9 ሚሊዮን ኩንታል ምርት እንደሚጠበቅ የዞኑ አስተዳዳሪ አብዱልሰላም ዋሪዮ ገለጹ።
የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ እና የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በቦረና ዞን የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ይገኛሉ።

በዛሬው ዕለትም በቦረና ዞን ድሬ ወረዳ በክላስተር የለማ ስንዴን ጎብኝተዋል።
የቦረና ዞን ዋና አስተዳዳሪ አብዱልሰላም ዋሪዮ ለከፍተኛ የስራ ሀላፊዎቹ ባደረጉት ገለጻ፤ በዞኑ ከሁለት ወራት በፊት ጀምሮ እስከ ሰኔ መጨረሻ ድረስ የክረምት ወራት የግብርና ልማት እየተከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
በዚህም 135 ሺህ ሄክታር መሬት በተለያዩ የዘር ዓይነቶች መሸፈኑን ገልጸው ከዚህ ውስጥም ከ56 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በክላስተር እየለማ መሆኑንና 5ሺህ ሄክታር በስንዴ ምርት መሸፈኑን ጠቁመዋል።
ስንዴ፣ ቦሎቄ፣ ጤፍ፣ ማሾ እና ሌሎች ሰብሎችን ማልማት መቻሉን በመግለፅ፥ ከዚህም 1 ነጥብ 9 ሚሊዮን ኩንታል ምርት እንደሚጠበቅ ተናግረዋል።
የቦረና ዞን አሁን ላይ በተሻለ ምርታማነት ላይ እንደሚገኝ ጠቅሰው፥ የአርብቶ አደሩ የስራ ባህል እየተቀየረ መሆኑን ጠቁመዋል።
ምርታማነት እንዲያድግም መንግስት የተለያዩ ድጋፎችን እያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።

በልማት ጉብኝቱ ከፕሬዝዳንት ሽመልስ አብዲሳ በተጨማሪ በብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ ከፍያለው ተፈራ እና ሌሎች የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።
አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...
Sep 14, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026