
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 25/2017(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን በክረምት ወራት በዘር ከተሸፈነው 135ሺህ ሄክታር መሬት 1 ነጥብ 9 ሚሊዮን ኩንታል ምርት እንደሚጠበቅ የዞኑ አስተዳዳሪ አብዱልሰላም ዋሪዮ ገለጹ።
የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ እና የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በቦረና ዞን የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ይገኛሉ።

በዛሬው ዕለትም በቦረና ዞን ድሬ ወረዳ በክላስተር የለማ ስንዴን ጎብኝተዋል።
የቦረና ዞን ዋና አስተዳዳሪ አብዱልሰላም ዋሪዮ ለከፍተኛ የስራ ሀላፊዎቹ ባደረጉት ገለጻ፤ በዞኑ ከሁለት ወራት በፊት ጀምሮ እስከ ሰኔ መጨረሻ ድረስ የክረምት ወራት የግብርና ልማት እየተከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
በዚህም 135 ሺህ ሄክታር መሬት በተለያዩ የዘር ዓይነቶች መሸፈኑን ገልጸው ከዚህ ውስጥም ከ56 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በክላስተር እየለማ መሆኑንና 5ሺህ ሄክታር በስንዴ ምርት መሸፈኑን ጠቁመዋል።
ስንዴ፣ ቦሎቄ፣ ጤፍ፣ ማሾ እና ሌሎች ሰብሎችን ማልማት መቻሉን በመግለፅ፥ ከዚህም 1 ነጥብ 9 ሚሊዮን ኩንታል ምርት እንደሚጠበቅ ተናግረዋል።
የቦረና ዞን አሁን ላይ በተሻለ ምርታማነት ላይ እንደሚገኝ ጠቅሰው፥ የአርብቶ አደሩ የስራ ባህል እየተቀየረ መሆኑን ጠቁመዋል።
ምርታማነት እንዲያድግም መንግስት የተለያዩ ድጋፎችን እያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።

በልማት ጉብኝቱ ከፕሬዝዳንት ሽመልስ አብዲሳ በተጨማሪ በብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ ከፍያለው ተፈራ እና ሌሎች የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026