
ወላይታ ሶዶ፤ሰኔ 25/2017 (ኢዜአ)፦በአደጋ ጊዜ ለሰብዓዊ ድጋፍ ደራሽ ለመሆን የዝግጁነት አቅምን ማጠናከር እንደሚገባ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የግብርና ቢሮ ኃላፊ መሪሁን ፍቅሩ (ዶ/ር) ገለጹ።
''ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለሀገር ሉዓላዊነትና ለተሟላ ክብር'' በሚል መሪ ሃሳብ ሰብአዊ ድጋፍን በራስ አቅም መሸፈን በሚቻልበት ሁኔታ ላይ የአመራሮች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በወላይታ ሶዶ ከተማ ተካሂዷል።

በመድረኩ ላይ የተገኙት መሪሁን ፍቅሩ (ዶ/ር)፤በአደጋ ጊዜ ለሰብዓዊ ድጋፍ ደራሽ ለመሆን የዝግጁነት አቅምን ማጠናከርና ማሳደግ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል።
ለዚህም በየደረጃው ያለው አመራር በቂ ግንዛቤ ኖሮች ለተግባራዊነቱ በቅንጅት መስራት ይጠበቅበታል ሲሉ ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ በምግብ ራሷን የሚያስችላት እምቅ አቅምና ሰፊ እድሎች ያሏት መሆኑን ያነሱት ዶክተር መሪሁን፤ በሁሉም መስኮች የተጀመሩ ተስፋ ሰጭ የልማት ጥረቶችን ማጠናከር ይገባል ብለዋል።
በግብርናም ይሁን በሌሎች ሴክተሮች ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ጥረቶች ተስፋ የተሰነቀባቸው መሆኑን አንስተው፥ በምርታማነት ከእርዳታ ጠባቂነት መውጣት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በክልሉ ባለፈዉ የበልግ ወቅት ለአደጋ ጊዜ መጠባበቂያ በተዘጋጁ መጋዝኖች ምርት የተከማቸባቸው መሆኑን ገልጸው፥በቀጣይም መጠናከር እንዳለበት አንስተዋል።

የክልሉ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር ጋንታ ጋምአ፤ በክልሉ የሚፈጠሩ አደጋዎችን በራስ አቅም ምላሽ መስጠትና መቋቋም የሚያስችል ዝግጁነት እንዲኖር እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በሌማት ትሩፋት፣በበጋ መስኖ ስንዴና በሌሎችም የግብርና እና የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት የምርታማነት አቅሞች እየተፈጠሩ መሆኑንም አንስተዋል።
በመድረኩ የክልል፣የዞን፣ የከተማ እና የወረዳ አስተዳደር አመራሮችና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026