
ወላይታ ሶዶ፤ሰኔ 25/2017 (ኢዜአ)፦በአደጋ ጊዜ ለሰብዓዊ ድጋፍ ደራሽ ለመሆን የዝግጁነት አቅምን ማጠናከር እንደሚገባ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የግብርና ቢሮ ኃላፊ መሪሁን ፍቅሩ (ዶ/ር) ገለጹ።
''ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለሀገር ሉዓላዊነትና ለተሟላ ክብር'' በሚል መሪ ሃሳብ ሰብአዊ ድጋፍን በራስ አቅም መሸፈን በሚቻልበት ሁኔታ ላይ የአመራሮች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በወላይታ ሶዶ ከተማ ተካሂዷል።

በመድረኩ ላይ የተገኙት መሪሁን ፍቅሩ (ዶ/ር)፤በአደጋ ጊዜ ለሰብዓዊ ድጋፍ ደራሽ ለመሆን የዝግጁነት አቅምን ማጠናከርና ማሳደግ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል።
ለዚህም በየደረጃው ያለው አመራር በቂ ግንዛቤ ኖሮች ለተግባራዊነቱ በቅንጅት መስራት ይጠበቅበታል ሲሉ ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ በምግብ ራሷን የሚያስችላት እምቅ አቅምና ሰፊ እድሎች ያሏት መሆኑን ያነሱት ዶክተር መሪሁን፤ በሁሉም መስኮች የተጀመሩ ተስፋ ሰጭ የልማት ጥረቶችን ማጠናከር ይገባል ብለዋል።
በግብርናም ይሁን በሌሎች ሴክተሮች ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ጥረቶች ተስፋ የተሰነቀባቸው መሆኑን አንስተው፥ በምርታማነት ከእርዳታ ጠባቂነት መውጣት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በክልሉ ባለፈዉ የበልግ ወቅት ለአደጋ ጊዜ መጠባበቂያ በተዘጋጁ መጋዝኖች ምርት የተከማቸባቸው መሆኑን ገልጸው፥በቀጣይም መጠናከር እንዳለበት አንስተዋል።

የክልሉ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር ጋንታ ጋምአ፤ በክልሉ የሚፈጠሩ አደጋዎችን በራስ አቅም ምላሽ መስጠትና መቋቋም የሚያስችል ዝግጁነት እንዲኖር እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በሌማት ትሩፋት፣በበጋ መስኖ ስንዴና በሌሎችም የግብርና እና የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት የምርታማነት አቅሞች እየተፈጠሩ መሆኑንም አንስተዋል።
በመድረኩ የክልል፣የዞን፣ የከተማ እና የወረዳ አስተዳደር አመራሮችና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026