ደሴ፤ሰኔ 25/2017(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በማዕድን ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን በአግባቡ በመለየት ጥቅም ላይ ለማዋል በተደረገው ጥረት ተጨባጭ ውጤት እየተመዘገበ መምጣቱን የክልሉ ማዕድን ሀብት ልማት ቢሮ አስታወቀ።
ቢሮው የተገኙ ውጤቶችን ለማስቀጠልና የሚስተዋሉ ክፍተቶችን ለመሙላት የሚያስችል ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ የምክክር መድረክ በኮምቦልቻ ከተማ ዛሬ አካሂዷል።
የቢሮ ኃላፊው አቶ ሀይሌ አበበ በመድረኩ ላይ እንደገለፁት፤ በክልሉ ከዩኒቨርሲቲዎች ጋር በመተባበር እየተካሄደ በሚገኘው ጥናት ከ50 ዓይነት በላይ የማዕድን ጸጋዎች እንዳሉ ተረጋግጧል።
የኮንስትራክሽን፣ኢንዱስትሪ፣ብረትና ብረት ነክ፣ የሀይል አማራጭ፣ የከበሩና ሌሎች የማዕድን ፀጋዎችን በመለየት ጥቅም ላይ ለማዋል በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
ለዘርፉ እድገትም የማእድን መገኛ ቦታዎችን ለይቶ በማስረከብ፣ ብድር ማመቻቸትና ሌሎችም ድጋፎች በዘርፉ ለሚሰማሩ ባለሃብቶች እየተደረገ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
በዚህም ባለፉት 11 ወራትም 113 ሚሊዮን ዶላር ተኪ ምርት በማምረት ለኢንዱስትሪዎች ግብአት መዋሉን ጠቁመው፥ 7 ነጥብ 8 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ከዘርፉ ማግኘት መቻሉን ገልጸዋል።
ዘርፉ ለ48 ሺህ ዜጎች የሥራ እድል በመፍጠርና ከሮያሊቲና ሌሎች የገቢ አርእስቶች 86 ሚሊዮን ብር ገቢ ማስገኘት መቻሉንም አስረድተዋል።
የደቡብ ወሎ ዞን ማዕድን ሀብት ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ አህመድ አበባው በበኩላቸው፥ በዞኑ 33 አይነት ማዕድኖች መኖራቸው በጥናት ተረጋግጦ ወደ ልማት መገባቱንም ገልጸዋል።
ባለፉት 11 ወራትም በማእድን ዘርፍ ለሚሰማሩ ለ325 ባለሃብቶች ፍቃድ መስጠት መቻሉን ጠቁመው፥ ከ5 ሺህ ለሚበልጡ ዜጎች የሥራ እድል ተፈጥሯል ብለዋል።
በዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችን በቅንጅት በመፍታት የተገኘውን ውጤት ለማስቀጠል እየተሰራ ነው ያሉት ደግሞ የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ማዕድን ሀብት ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሲራጅ ጀማል ናቸው።
መንግስት በሰጠው ትኩረት በማዕድን ዘርፉ ተኪ ምርት በማምረት፣ የውጭ ምንዛሬ በማስገኘት፣ ለዜጎች የሥራ እድል መፍጠር ተችሏል ብለዋል።
በምክክር መድረኩ የክልል፣የደቡብ ወሎ፣የኦሮሞ ብሔረሰብ ዞኖች፣ እንዲሁም የደሴና የኮምቦልቻ ከተማ አመራሮች፣የዘርፉ ባለሀብቶችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025
ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...
Feb 28, 2025
ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...
Feb 24, 2025