የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በክልሉ የማእድን ፀጋዎችን በአግባቡ በመለየት ጥቅም ላይ ለማዋል የተደረገው ጥረት ውጤት እያመጣ ነው -ቢሮው

Jul 3, 2025

IDOPRESS

ደሴ፤ሰኔ 25/2017(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በማዕድን ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን በአግባቡ በመለየት ጥቅም ላይ ለማዋል በተደረገው ጥረት ተጨባጭ ውጤት እየተመዘገበ መምጣቱን የክልሉ ማዕድን ሀብት ልማት ቢሮ አስታወቀ።

ቢሮው የተገኙ ውጤቶችን ለማስቀጠልና የሚስተዋሉ ክፍተቶችን ለመሙላት የሚያስችል ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ የምክክር መድረክ በኮምቦልቻ ከተማ ዛሬ አካሂዷል።


የቢሮ ኃላፊው አቶ ሀይሌ አበበ በመድረኩ ላይ እንደገለፁት፤ በክልሉ ከዩኒቨርሲቲዎች ጋር በመተባበር እየተካሄደ በሚገኘው ጥናት ከ50 ዓይነት በላይ የማዕድን ጸጋዎች እንዳሉ ተረጋግጧል።

የኮንስትራክሽን፣ኢንዱስትሪ፣ብረትና ብረት ነክ፣ የሀይል አማራጭ፣ የከበሩና ሌሎች የማዕድን ፀጋዎችን በመለየት ጥቅም ላይ ለማዋል በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

ለዘርፉ እድገትም የማእድን መገኛ ቦታዎችን ለይቶ በማስረከብ፣ ብድር ማመቻቸትና ሌሎችም ድጋፎች በዘርፉ ለሚሰማሩ ባለሃብቶች እየተደረገ እንደሚገኝ አስረድተዋል።

በዚህም ባለፉት 11 ወራትም 113 ሚሊዮን ዶላር ተኪ ምርት በማምረት ለኢንዱስትሪዎች ግብአት መዋሉን ጠቁመው፥ 7 ነጥብ 8 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ከዘርፉ ማግኘት መቻሉን ገልጸዋል።

ዘርፉ ለ48 ሺህ ዜጎች የሥራ እድል በመፍጠርና ከሮያሊቲና ሌሎች የገቢ አርእስቶች 86 ሚሊዮን ብር ገቢ ማስገኘት መቻሉንም አስረድተዋል።


የደቡብ ወሎ ዞን ማዕድን ሀብት ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ አህመድ አበባው በበኩላቸው፥ በዞኑ 33 አይነት ማዕድኖች መኖራቸው በጥናት ተረጋግጦ ወደ ልማት መገባቱንም ገልጸዋል።

ባለፉት 11 ወራትም በማእድን ዘርፍ ለሚሰማሩ ለ325 ባለሃብቶች ፍቃድ መስጠት መቻሉን ጠቁመው፥ ከ5 ሺህ ለሚበልጡ ዜጎች የሥራ እድል ተፈጥሯል ብለዋል።

በዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችን በቅንጅት በመፍታት የተገኘውን ውጤት ለማስቀጠል እየተሰራ ነው ያሉት ደግሞ የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ማዕድን ሀብት ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሲራጅ ጀማል ናቸው።


መንግስት በሰጠው ትኩረት በማዕድን ዘርፉ ተኪ ምርት በማምረት፣ የውጭ ምንዛሬ በማስገኘት፣ ለዜጎች የሥራ እድል መፍጠር ተችሏል ብለዋል።

በምክክር መድረኩ የክልል፣የደቡብ ወሎ፣የኦሮሞ ብሔረሰብ ዞኖች፣ እንዲሁም የደሴና የኮምቦልቻ ከተማ አመራሮች፣የዘርፉ ባለሀብቶችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢንዱስትሪ ፓርኩ መገንባት መንግሥት ለዘርፉ የሰጠውን ትኩረት በተጨባጭ ያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...

May 20, 2026

የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል 

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...

May 7, 2026

የከተማዋን ባህል፣ ታሪክ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በማልማት ለኢኮኖሚያዊ ጥቅም የማዋል ተግባራት ይጠናከራሉ

ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...

May 7, 2026

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026