የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በምስራቅ ጎጃም ዞን ገቢን በአግባቡ በመሰብሰብ ለህዝብ የልማት ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት እየተሰራ ነው

Jul 8, 2025

IDOPRESS

ደብረ ማርቆስ፤ ሰኔ 30/2017 (ኢዜአ)፦ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ በአግባቡ በመሰብሰብ ለህዝብ የልማት ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት እየተሰራ መሆኑን የምስራቅ ጎጃም ዞን አስተዳደር አስታወቀ።

የምስራቅ ጎጃም ዞን ገቢዎች መምሪያ የበጀት ዓመቱ የገቢ ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማና የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ያተኮረ የንቅናቄ መድረክ በደጀን ከተማ ተካሂዷል።

የምስራቅ ጎጃም ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ኑርልኝ ብርሃኑ በወቅቱ እንደገለጹት ገቢን በአግባቡ በመሰብሰብ ለህብረተሰቡ የልማት ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት በሚደረገው ጥረት የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ ወሳኝ ነው።

ቀደም ሲል በአካባቢው አጋጥሞ በነበረው የጸጥታ ችግር ገቢን አሟጦ ለመሰብሰብ ውስንነት እንደነበር አስታውሰው፣

ችግሩን በቅንጅት ለመፍታት በተደረገ ጥረት የተሻለ ገቢ መሰብሰቡንና የባለድርሻ አካላት አስተዋጽኦም የጎላ መሆኑን ገልጸዋል።

የምስራቅ ጎጃም ዞን ገቢዎች መምሪያ ሃላፊ ወይዘሮ ጥሩምርት አለልኝ እንዳሉት ዞኑ የሚያመነጨውን ገቢ ለመሰብሰብ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው።

በዚህም በበጀት ዓመቱ ከተለያዩ የገቢ አርስቶች ከ3 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ ለመሰብሰብ ታቅዶ ከ2 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ ለመሰብሰብ መቻሉን ተናግረዋል።

የተሰበሰበው ገቢ ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር 86 በመቶ ብልጫ እንዳለው ጠቅሰዋል።

በየደረጃው ያለው አመራርና የዘርፉ ባለሙያዎች ለገቢ አሰባሰቡ ትኩረት ሰጥተው በቅንጅት መስራታቸው ለብልጫው የራሱን አስተዋጽኦ ማድረጉንም ጠቁመዋል።

ይህም የዞኑን ዓመታዊ ወጭ 22 ነጥብ 6 በመቶ የመሸፈን አቅም እንዳለው ጠቁመው ገቢው ከ37 ሺህ በላይ ግብር ከፋዮች የተሰበሰበ መሆኑን ተናግረዋል።

በዞኑ የእነማይ ወረዳ ገቢዎች ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ አያሌው መላኩ በበኩላቸው እንዳሉት፣ በየደረጃው ያለው አመራር ለግብር መሰብሰብ ትኩረት ሰጥቶ በመስራቱ ውጤታማ ሥራ ተሰርቷል።


በበጀት ዓመቱ በወረዳው ከ85 ሚሊዮን ብር በላይ ለመሰብሰብ ታቅዶ ከ90 ሚሊዮን ብር በላይ ለመሰብሰብ መቻሉን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025