🔇Unmute
ዲላ፤ መስከረም 19/2018(ኢዜአ) ፡- በተያዘው ዓመት ቡናን በጥራትና በብዛት በማምረት ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን ለማሳደግ ግብ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ገለፀ።
በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የዲላ ቡና ምርት ጥራት ምርመራና ሰርተፍኬሽን ማዕከል ዛሬ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል።

ማዕከሉ በክልሉ የመጀመሪያው ሲሆን ፤ የንግድ ሰንሰለትን በመቀነስ የቡና አቅራቢውን እንግልት የሚቀንስ መሆኑም ተመላክቷል።
ማዕከሉን መርቀው የከፈቱት የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አዱኛ ደበላ (ዶ/ር)፤ በተያዘው ዓመት ቡናን በጥራትና በብዛት ለዓለም ገበያ ለማቅረብ ጥረት እየተደረገ ነው ብለዋል።
ለዚህም የቡና ምርት ጥራት ምርመራና ሰርተፍኬሽን ማዕከላትን ማስፋት ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው፣ በተለይ በልዩ ጣዕሙ የሚታወቀው የይርጋጨፌ ቡናን ተፈጥሯዊ ጣዕሙን ጠብቆ ለዓለም ገበያ እንዲቀርብ አጋዥ መሆኑን ገልፀዋል።
ማዕከሉ በሙሉ አቅሙ እንዲሠራ የምርት አቅርቦት ላይ በትኩረት መስራት እንደሚገባም አስገንዝበዋል።
ክልሉ ለቡና ልማት ምቹ ስነምህዳር እንዳለው የገለጹት ደግሞ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አበባየሁ ታደሰ ( ዶ/ር ) ናቸው።

ለዚህም የይርጋጨፌ ፣ አማሮና ሌሎች ቡናዎች ተጠቃሽ መሆናቸውን አንስተው፤ ማዕከሉ የቡና ጥራትን ከማስጠበቅ ባለፈ የምርምርና ስልጠና ማዕከል በመሆን አርሶ አደሩን ማገዝ እንዲችል ይስራል ብለዋል።
በተለይም በቡና ግብይት ወቅት የሚስተዋሉ ተግዳሮቶችን በመፍታት ቀልጣፋ አሰራር መፍጠር እንደሚገባም አስገንዝበዋል።
የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ(ዶ/ር) በበኩላቸው ፤ በዞኑ በቡና እድሳት የተከናወኑ ተግባራት በቡና ምርትና ጥራት ላይ አስተዋጽኦ አበርክተዋል።

በዘርፉ የአምራች አርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በቀጥታ የውጪ ንግድ ትስስር ተሳትፎውን ለማሳደግ እየተሠራ ነው ብለዋል።
ማዕከሉ በዲላ ከተማ ሥራ መጀመሩ የንግድ ሰንሰለቱን ቀልጣፋ በማድረግ ለውጪ ገበያ የሚቀርበውን የቡና ምርት መጠን የሚያሳድግ መሆኑን ገልፀዋል።
የማዕከሉ መገንባት ለረጅም ጊዜ ጥያቄያችን ምላሽ የሰጠ ነው ያሉት ደግሞ የጌዴኦ ዞን የቡና አቅራቢዎች ማህበር ሰብሳቢ አቶ ኢያሱ ወራሳ ናቸው።

በተለይም ማዕከሉ በቅርበት መከፈቱ የተራዘመ የንግድ ሰንሰለትን በመቀነስ የትራንስፖርት ወጪና የጊዜ ብክነትን የሚያስቀር መሆኑን አስረድተዋል።
ማህበሩ ከ17 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ ማዕከሉ የሚጠበቅበትን መስፈርት እንዲያሟላ መደረጉን አንስተው፤ ይህም ማህበሩ ወደ ላኪነት ለማደግ የሚያደረገውን ጥርት ያጠናክራል ብለዋል።
በመረሃ ገብሩ ላይ የፌዴራል፣ የክልልና የዞን ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች፣ አርሶ አደሮች፣ አቅራቢዎችና የዘርፉ ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...
Sep 14, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026