የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ቡናን በጥራትና በብዛት በማምረት ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን ማሳደግ የሚያችስሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው - ባለስልጣኑ

Sep 30, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ዲላ፤ መስከረም 19/2018(ኢዜአ) ፡- በተያዘው ዓመት ቡናን በጥራትና በብዛት በማምረት ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን ለማሳደግ ግብ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ገለፀ።

በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የዲላ ቡና ምርት ጥራት ምርመራና ሰርተፍኬሽን ማዕከል ዛሬ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል።


ማዕከሉ በክልሉ የመጀመሪያው ሲሆን ፤ የንግድ ሰንሰለትን በመቀነስ የቡና አቅራቢውን እንግልት የሚቀንስ መሆኑም ተመላክቷል።

ማዕከሉን መርቀው የከፈቱት የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አዱኛ ደበላ (ዶ/ር)፤ በተያዘው ዓመት ቡናን በጥራትና በብዛት ለዓለም ገበያ ለማቅረብ ጥረት እየተደረገ ነው ብለዋል።

ለዚህም የቡና ምርት ጥራት ምርመራና ሰርተፍኬሽን ማዕከላትን ማስፋት ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው፣ በተለይ በልዩ ጣዕሙ የሚታወቀው የይርጋጨፌ ቡናን ተፈጥሯዊ ጣዕሙን ጠብቆ ለዓለም ገበያ እንዲቀርብ አጋዥ መሆኑን ገልፀዋል።

ማዕከሉ በሙሉ አቅሙ እንዲሠራ የምርት አቅርቦት ላይ በትኩረት መስራት እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

ክልሉ ለቡና ልማት ምቹ ስነምህዳር እንዳለው የገለጹት ደግሞ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አበባየሁ ታደሰ ( ዶ/ር ) ናቸው።


ለዚህም የይርጋጨፌ ፣ አማሮና ሌሎች ቡናዎች ተጠቃሽ መሆናቸውን አንስተው፤ ማዕከሉ የቡና ጥራትን ከማስጠበቅ ባለፈ የምርምርና ስልጠና ማዕከል በመሆን አርሶ አደሩን ማገዝ እንዲችል ይስራል ብለዋል።

በተለይም በቡና ግብይት ወቅት የሚስተዋሉ ተግዳሮቶችን በመፍታት ቀልጣፋ አሰራር መፍጠር እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ(ዶ/ር) በበኩላቸው ፤ በዞኑ በቡና እድሳት የተከናወኑ ተግባራት በቡና ምርትና ጥራት ላይ አስተዋጽኦ አበርክተዋል።


በዘርፉ የአምራች አርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በቀጥታ የውጪ ንግድ ትስስር ተሳትፎውን ለማሳደግ እየተሠራ ነው ብለዋል።

ማዕከሉ በዲላ ከተማ ሥራ መጀመሩ የንግድ ሰንሰለቱን ቀልጣፋ በማድረግ ለውጪ ገበያ የሚቀርበውን የቡና ምርት መጠን የሚያሳድግ መሆኑን ገልፀዋል።

የማዕከሉ መገንባት ለረጅም ጊዜ ጥያቄያችን ምላሽ የሰጠ ነው ያሉት ደግሞ የጌዴኦ ዞን የቡና አቅራቢዎች ማህበር ሰብሳቢ አቶ ኢያሱ ወራሳ ናቸው።


በተለይም ማዕከሉ በቅርበት መከፈቱ የተራዘመ የንግድ ሰንሰለትን በመቀነስ የትራንስፖርት ወጪና የጊዜ ብክነትን የሚያስቀር መሆኑን አስረድተዋል።

ማህበሩ ከ17 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ ማዕከሉ የሚጠበቅበትን መስፈርት እንዲያሟላ መደረጉን አንስተው፤ ይህም ማህበሩ ወደ ላኪነት ለማደግ የሚያደረገውን ጥርት ያጠናክራል ብለዋል።

በመረሃ ገብሩ ላይ የፌዴራል፣ የክልልና የዞን ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች፣ አርሶ አደሮች፣ አቅራቢዎችና የዘርፉ ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026