🔇Unmute
ወልዲያ፤ጥቅምት 2/2018(ኢዜአ)፦የወልድያ ከተማ የመጀመሪያው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ግንባታ በመገባደድ ላይ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ።
የወልዲያ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ንጉስ ዝናቡ፤ በከተማዋ የመጀመሪያው ምእራፍ የኮሪደር ልማት ከአዳጎ አደባባይ በመነሳት እስከ ጎንደር በር ግንባታው በመጠናቀቅ ላይ መሆኑን ገልጸዋል።
አሁን ላይ አፈፃፀሙ ከ96 በመቶ በላይ መድረሱን አንስተው፥ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተመርቆ ለአገልግሎት የሚበቃ ይሆናል ብለዋል።
የኮሪደር ልማቱ የአስፋልት መንገድ ግንባታና የእግረኛ መንገድን ጨምሮ አረንጓዴና የመዝናኛ ስፍራዎችን ያካተተ መሆኑን አንስተው፥ በጥራትና በፍጥነት መከናወኑንም ተናግረዋል።
በዚህም ከ300 በላይ ለሆኑ ወገኖች የስራ ዕድል የፈጠረ መሆኑን አንስተው፥ ከተማዋን የማልማት ስራ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑንም አረጋግጠዋል።
ከከተማዋ ነዋሪዎች መካከል አቶ ፍስሃ መንግስቴ እና ወይዘሮ አልማዝ አያሌው፤ የኮሪደር ልማቱ ከተማዋን ውብና ለኑሮ ምቹ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
ልማቱ ለነዋሪዎች፣ ለጎብኝዎች፣ ለባለሃብቶችና ሌሎች አገልግሎት ሰጭዎች ምቹ አካባቢን የፈጠረ በመሆኑ የሚደነቅ ስራ ነው ብለዋል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026