🔇Unmute
ወልዲያ፤ጥቅምት 2/2018(ኢዜአ)፦የወልድያ ከተማ የመጀመሪያው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ግንባታ በመገባደድ ላይ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ።
የወልዲያ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ንጉስ ዝናቡ፤ በከተማዋ የመጀመሪያው ምእራፍ የኮሪደር ልማት ከአዳጎ አደባባይ በመነሳት እስከ ጎንደር በር ግንባታው በመጠናቀቅ ላይ መሆኑን ገልጸዋል።
አሁን ላይ አፈፃፀሙ ከ96 በመቶ በላይ መድረሱን አንስተው፥ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተመርቆ ለአገልግሎት የሚበቃ ይሆናል ብለዋል።
የኮሪደር ልማቱ የአስፋልት መንገድ ግንባታና የእግረኛ መንገድን ጨምሮ አረንጓዴና የመዝናኛ ስፍራዎችን ያካተተ መሆኑን አንስተው፥ በጥራትና በፍጥነት መከናወኑንም ተናግረዋል።
በዚህም ከ300 በላይ ለሆኑ ወገኖች የስራ ዕድል የፈጠረ መሆኑን አንስተው፥ ከተማዋን የማልማት ስራ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑንም አረጋግጠዋል።
ከከተማዋ ነዋሪዎች መካከል አቶ ፍስሃ መንግስቴ እና ወይዘሮ አልማዝ አያሌው፤ የኮሪደር ልማቱ ከተማዋን ውብና ለኑሮ ምቹ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
ልማቱ ለነዋሪዎች፣ ለጎብኝዎች፣ ለባለሃብቶችና ሌሎች አገልግሎት ሰጭዎች ምቹ አካባቢን የፈጠረ በመሆኑ የሚደነቅ ስራ ነው ብለዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025
ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...
Feb 28, 2025
ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...
Feb 24, 2025