🔇Unmute
ወልዲያ፤ጥቅምት 2/2018(ኢዜአ)፦የወልድያ ከተማ የመጀመሪያው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ግንባታ በመገባደድ ላይ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ።
የወልዲያ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ንጉስ ዝናቡ፤ በከተማዋ የመጀመሪያው ምእራፍ የኮሪደር ልማት ከአዳጎ አደባባይ በመነሳት እስከ ጎንደር በር ግንባታው በመጠናቀቅ ላይ መሆኑን ገልጸዋል።
አሁን ላይ አፈፃፀሙ ከ96 በመቶ በላይ መድረሱን አንስተው፥ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተመርቆ ለአገልግሎት የሚበቃ ይሆናል ብለዋል።
የኮሪደር ልማቱ የአስፋልት መንገድ ግንባታና የእግረኛ መንገድን ጨምሮ አረንጓዴና የመዝናኛ ስፍራዎችን ያካተተ መሆኑን አንስተው፥ በጥራትና በፍጥነት መከናወኑንም ተናግረዋል።
በዚህም ከ300 በላይ ለሆኑ ወገኖች የስራ ዕድል የፈጠረ መሆኑን አንስተው፥ ከተማዋን የማልማት ስራ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑንም አረጋግጠዋል።
ከከተማዋ ነዋሪዎች መካከል አቶ ፍስሃ መንግስቴ እና ወይዘሮ አልማዝ አያሌው፤ የኮሪደር ልማቱ ከተማዋን ውብና ለኑሮ ምቹ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
ልማቱ ለነዋሪዎች፣ ለጎብኝዎች፣ ለባለሃብቶችና ሌሎች አገልግሎት ሰጭዎች ምቹ አካባቢን የፈጠረ በመሆኑ የሚደነቅ ስራ ነው ብለዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026