🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 2/2018(ኢዜአ)፦ግብርና የሀገር ኢኮኖሚን በመገንባት፣በመቀየር እና ከማሸጋገር አኳያ ቁልፍ ሚና እየተወጣ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለጹ።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ የ2017 አፈጻጸም ማጠቃለያ ጉባኤ እና የ2018 የበጋ ወቅት የተቀናጀ የግብርና ስራዎች ንቅናቄ መድረክ በዱራሜ ከተማ እያካሄደ ይገኛል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻዉ ጣሰው (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፤ ኢትዮጵያ በ2018 ከተስፋ ብርሃን ወደሚጨበጥ ተስፋ ለመሸጋገር የያዘችውን ዕቅድ ተግባራዊ ማድረግ የሚያስችሉ ስራዎች እየተሰሩ ነው።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሁሉም ዘርፎች የታቀዱ ስራዎች ለውጥ እየታየባቸው መሆኑን ጠቁመው፥ በግብርናው ዘርፍ የቴክኖሎጂ ሽግግርን ለማሣካት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።
በክልሉ በሁሉም ዘርፍ ማለትም በግብርና፣የማኑፋክቸሪንግ ፣በቱሪዝም ፣ በማዕድን ሀብቶችን በአግባቡ መጠቀም እንዲሁም ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
ግብርና የአገር ኢኮኖሚን መገንባት ብቻ ሳይሆን በመቀየር እና በማሸጋገር ሂደት የሚኖረው አበርክቶ የላቀ ስለመሆኑም ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቅሰዋል።

የቤተሰብ ብልጽግናን በገጠር እና በከተማ ለማረጋገጥ ወሳኝ ሚና ካላቸው ዘርፎች ውስጥ ግብርና ወሳኝ ሚና እንዳለውም ርዕሰ መስተዳድሩ ተናግረዋል።
በክልሉ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ተረጂነትን ለማስቀረት እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ውጤት ማስገኘታቸውን ጠቁመዋል።
በግብርና ወጪ ምርቶችን በብዛትና ጥራት ማምረት፣ ገቢ ምርቶችን ለመተካት እንዲሁም በዘርፉ የሥራ ዕድል ፈጠራን እውን ለማድረግ እየተሰራ እንደሚገኝም ገልጸዋል።
ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችም ተስፋ ሰጪ ውጤት እየተመዘገበባቸው መሆኑንም ጠቁመዋል።
አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...
Sep 14, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026