🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 2/2018(ኢዜአ)፦ግብርና የሀገር ኢኮኖሚን በመገንባት፣በመቀየር እና ከማሸጋገር አኳያ ቁልፍ ሚና እየተወጣ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለጹ።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ የ2017 አፈጻጸም ማጠቃለያ ጉባኤ እና የ2018 የበጋ ወቅት የተቀናጀ የግብርና ስራዎች ንቅናቄ መድረክ በዱራሜ ከተማ እያካሄደ ይገኛል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻዉ ጣሰው (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፤ ኢትዮጵያ በ2018 ከተስፋ ብርሃን ወደሚጨበጥ ተስፋ ለመሸጋገር የያዘችውን ዕቅድ ተግባራዊ ማድረግ የሚያስችሉ ስራዎች እየተሰሩ ነው።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሁሉም ዘርፎች የታቀዱ ስራዎች ለውጥ እየታየባቸው መሆኑን ጠቁመው፥ በግብርናው ዘርፍ የቴክኖሎጂ ሽግግርን ለማሣካት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።
በክልሉ በሁሉም ዘርፍ ማለትም በግብርና፣የማኑፋክቸሪንግ ፣በቱሪዝም ፣ በማዕድን ሀብቶችን በአግባቡ መጠቀም እንዲሁም ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
ግብርና የአገር ኢኮኖሚን መገንባት ብቻ ሳይሆን በመቀየር እና በማሸጋገር ሂደት የሚኖረው አበርክቶ የላቀ ስለመሆኑም ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቅሰዋል።

የቤተሰብ ብልጽግናን በገጠር እና በከተማ ለማረጋገጥ ወሳኝ ሚና ካላቸው ዘርፎች ውስጥ ግብርና ወሳኝ ሚና እንዳለውም ርዕሰ መስተዳድሩ ተናግረዋል።
በክልሉ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ተረጂነትን ለማስቀረት እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ውጤት ማስገኘታቸውን ጠቁመዋል።
በግብርና ወጪ ምርቶችን በብዛትና ጥራት ማምረት፣ ገቢ ምርቶችን ለመተካት እንዲሁም በዘርፉ የሥራ ዕድል ፈጠራን እውን ለማድረግ እየተሰራ እንደሚገኝም ገልጸዋል።
ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችም ተስፋ ሰጪ ውጤት እየተመዘገበባቸው መሆኑንም ጠቁመዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026