የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ያለውን እምቅ የተፈጥሮ ሀብት በማልማት የኢኮኖሚ ጠቀሜታውን ለማሳደግ እየተሰራ ነው-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻዉ ጣሰው (ዶ/ር)

Oct 13, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ጥቅምት 2/2018(ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ያለውን እምቅ የተፈጥሮ ሀብት በማልማት የኢኮኖሚ ጠቀሜታውን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻዉ ጣሰው (ዶ/ር) ገለጹ።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ የ2017 አፈጻጸም እና የ2018 የበጋ ወቅት የተቀናጀ የግብርና ልማት ሥራዎች ንቅናቄ መድረክ በዱራሜ ከተማ ተካሂዷል።


የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻዉ ጣሰው (ዶ/ር) በንቅናቄ መድረኩ ማጠቃለያ በሰጡት የስራ መመሪያ እንደገለጹት፤ በክልሉ ያለውን እምቅ የተፈጥሮ ሀብት ኢኮኖሚ ጠቀሜታ ለማሳደግ እየተሰራ ነው።

የክልሉ መንግስት የግብርናና የኢንቨስትመንት አማራጮችን በማሳፋትም ለስራ እድል ፈጠራ ለማዋል ትኩረት መስጠቱን አስረድተዋል።

ለተግባራዊነቱም ጥራት ያለው እቅድ ማዘጋጀትና በቅንጅት መተግበር ተገቢ መሆኑን ተናግረዋል።

በተለይም ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የግብርናውን ኢኮኖሚ አቅም እውን ማድረግ እንደሚገባ ጠቁመዋል።

ለዚህም ግብዓቶችን ተደራሽ ማድረግ፣የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን መጠቀምና የጥናትና ምርምር ስራዎችን ወደ ተግባር መቀየር ተገቢ ስለመሆኑም አብራርተዋል።

አርሶ አደሩን በቅርበት የሚደግፉ ባለሙያዎች ሙሉ አቅማቸውን ተጠቅመው እንዲሰሩ ማድረግ ላይ ማተኮር ይገባል ሲሉም ጠቁመዋል።

በክልሉ የኤክስፖርት ምርት ማሳደግና፣ተኪ ምርቶችን በማምረት በገጠር እና በከተማ ለወጣቶች የስራ እድል መፍጠር ላይ ማተኮር እንደሚገባም ርዕሰ መስተዳድሩ አሳስበዋል።


የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ መለሰ መኮንን (ዶ/ር ) በበኩላቸው፤ የሀገርን ሀብት ታሳቢ ያደረገ የግብርና የኢኮኖሚ ሪፎርም ተግባራዊ እየተደረገ ነው ብለዋል።

በግብርናው ዘርፍ በሀገር እና በቤተሰብ የምግብ እና የስርዓተ ምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥም የፖሊሲው ዓላማ መሆኑን ጠቁመዋል።

የኤክስፖርት ምርትን በአይነት፣ በመጠንና በጥራት በማምረት ላይ እንዲሁም ተኪምርቶችን ማስፋትም የትኩረቱ አካል መሆኑን ሚኒስትር ዴኤታው አስገንዝበዋል።

የግብርናውን ዘርፍ ለስራ እድል ፈጠራና የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚተገበሩ ኢኒሼቲቮች ማሳካት እንደሚገባም ጠቁመዋል።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የገጠር ልማት ክላስተር አስተባባሪና ክልሉ ግብርና ቢሮ ሃላፊ አቶ ኡስማን ሱሩር እንደገለጹት ለግብርናው ዘርፍ መዘመን በዋነኛነት የአርሶ አደር ማሰልጠኛ ተቋማት ድርሻ ከፍተኛ ነው።

ተቋማቱ የምርምር ስራዎችን ለአርሶ አደሩ ተደራሽ በማድረግ ድህነትን ለማሸነፍ በሚደረገው ጥረት ድርሻቸውን እንዲያጠናክሩም አሳስበዋል።

በመድረኩ በ2017 በጀት ዓመት የላቀ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ተቋማትና ግለሰቦች የማበረታቻ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025