🔇Unmute
አምቦ፤ መስከረም /2018 (ኢዜአ)፦ በምዕራብ ሸዋ ዞን በመኸር ወቅት ከ16 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች በቅባት እህል ልማት ላይ መሳተፋቸውን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ፡፡
በዞኑ በመኸር ወቅት በቅባት እህል ዘር ከተሸፈነው ከ31 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ከ954 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት ይጠበቃል፡፡
በጽህፈት ቤቱ የአዝዕርት ልማት ባለሙያ አቶ ደጀኔ ደቡሼ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በዞኑ በመኸር ወቅት ለቅባት እህሎች ትኩረት በመስጠት ሰፊ ስራዎች ተሰርተዋል።
በዚህም በመኸር ወቅት ከ16 ሺህ በላይ አርሶ አደሮችን በማሳተፍ ከ31 ሺህ ሄክታር በላይ መሬትን በቅባት እህል ማልማት መቻሉን ገልጸዋል።
የቅባት እህል ምርቱ ባለፈው ዓመት በመኸር ወቅት ከለማው ብልጫ እንዳለው ጠቁመው ከዚህም ከ954 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅም አቶ ደጀኔ ተናግረዋል።
አርሶ አደሮቹም ዘመናዊ የእርሻ መሳሪያዎችን እንዲጠቀሙ ከማድረግ ባለፈ የግብርና ባለሙያ ድጋፍና ክትትል እየተደረገላቸው መሆኑን አስረድተዋል።
በተጨማሪም ዘርፉን በማጠናከር ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ከግብርና ምርምር ማዕከላት የተለቀቁ የተሻሻሉ የቅባት እህል ዝርያዎችን ለአርሶ አደሩ እንዲሰራጩና ጥቅም ላይ እንዲውሉ ማድረግ መቻሉን አንስተዋል።
እየለሙ ካሉ የቅባት እህሎች መካከል ኑግ፣ ተልባ፣ ሰሊጥ፣ ጎመን ዘርና ለውዝ በስፋት እንደሚገኙበትም ጠቅሰዋል፡፡
የቅባት እህል ምርቱ በዞኑ በተለይም በባኮ፣ በጮቢ፣ በግንደ በረት፣ በኢልፈታ፣ በጀልዱና በኖኖ ወረዳዎች በስፋት እየተመረተ መሆኑም ተገልጿል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026