🔇Unmute
አምቦ፤ መስከረም /2018 (ኢዜአ)፦ በምዕራብ ሸዋ ዞን በመኸር ወቅት ከ16 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች በቅባት እህል ልማት ላይ መሳተፋቸውን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ፡፡
በዞኑ በመኸር ወቅት በቅባት እህል ዘር ከተሸፈነው ከ31 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ከ954 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት ይጠበቃል፡፡
በጽህፈት ቤቱ የአዝዕርት ልማት ባለሙያ አቶ ደጀኔ ደቡሼ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በዞኑ በመኸር ወቅት ለቅባት እህሎች ትኩረት በመስጠት ሰፊ ስራዎች ተሰርተዋል።
በዚህም በመኸር ወቅት ከ16 ሺህ በላይ አርሶ አደሮችን በማሳተፍ ከ31 ሺህ ሄክታር በላይ መሬትን በቅባት እህል ማልማት መቻሉን ገልጸዋል።
የቅባት እህል ምርቱ ባለፈው ዓመት በመኸር ወቅት ከለማው ብልጫ እንዳለው ጠቁመው ከዚህም ከ954 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅም አቶ ደጀኔ ተናግረዋል።
አርሶ አደሮቹም ዘመናዊ የእርሻ መሳሪያዎችን እንዲጠቀሙ ከማድረግ ባለፈ የግብርና ባለሙያ ድጋፍና ክትትል እየተደረገላቸው መሆኑን አስረድተዋል።
በተጨማሪም ዘርፉን በማጠናከር ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ከግብርና ምርምር ማዕከላት የተለቀቁ የተሻሻሉ የቅባት እህል ዝርያዎችን ለአርሶ አደሩ እንዲሰራጩና ጥቅም ላይ እንዲውሉ ማድረግ መቻሉን አንስተዋል።
እየለሙ ካሉ የቅባት እህሎች መካከል ኑግ፣ ተልባ፣ ሰሊጥ፣ ጎመን ዘርና ለውዝ በስፋት እንደሚገኙበትም ጠቅሰዋል፡፡
የቅባት እህል ምርቱ በዞኑ በተለይም በባኮ፣ በጮቢ፣ በግንደ በረት፣ በኢልፈታ፣ በጀልዱና በኖኖ ወረዳዎች በስፋት እየተመረተ መሆኑም ተገልጿል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026