🔇Unmute
አምቦ፤ መስከረም /2018 (ኢዜአ)፦ በምዕራብ ሸዋ ዞን በመኸር ወቅት ከ16 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች በቅባት እህል ልማት ላይ መሳተፋቸውን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ፡፡
በዞኑ በመኸር ወቅት በቅባት እህል ዘር ከተሸፈነው ከ31 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ከ954 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት ይጠበቃል፡፡
በጽህፈት ቤቱ የአዝዕርት ልማት ባለሙያ አቶ ደጀኔ ደቡሼ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በዞኑ በመኸር ወቅት ለቅባት እህሎች ትኩረት በመስጠት ሰፊ ስራዎች ተሰርተዋል።
በዚህም በመኸር ወቅት ከ16 ሺህ በላይ አርሶ አደሮችን በማሳተፍ ከ31 ሺህ ሄክታር በላይ መሬትን በቅባት እህል ማልማት መቻሉን ገልጸዋል።
የቅባት እህል ምርቱ ባለፈው ዓመት በመኸር ወቅት ከለማው ብልጫ እንዳለው ጠቁመው ከዚህም ከ954 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅም አቶ ደጀኔ ተናግረዋል።
አርሶ አደሮቹም ዘመናዊ የእርሻ መሳሪያዎችን እንዲጠቀሙ ከማድረግ ባለፈ የግብርና ባለሙያ ድጋፍና ክትትል እየተደረገላቸው መሆኑን አስረድተዋል።
በተጨማሪም ዘርፉን በማጠናከር ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ከግብርና ምርምር ማዕከላት የተለቀቁ የተሻሻሉ የቅባት እህል ዝርያዎችን ለአርሶ አደሩ እንዲሰራጩና ጥቅም ላይ እንዲውሉ ማድረግ መቻሉን አንስተዋል።
እየለሙ ካሉ የቅባት እህሎች መካከል ኑግ፣ ተልባ፣ ሰሊጥ፣ ጎመን ዘርና ለውዝ በስፋት እንደሚገኙበትም ጠቅሰዋል፡፡
የቅባት እህል ምርቱ በዞኑ በተለይም በባኮ፣ በጮቢ፣ በግንደ በረት፣ በኢልፈታ፣ በጀልዱና በኖኖ ወረዳዎች በስፋት እየተመረተ መሆኑም ተገልጿል።
አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...
Sep 14, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026