የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ወገኖች በምግብ ዋስትና ፕሮግራም ታቅፈው ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እያሳደጉ ነው 

Oct 15, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ኮምቦልቻ ፤ ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ) ፡-በኮምቦልቻ ከተማ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ወገኖች በምግብ ዋስትና ፕሮግራም ታቅፈው በተደረገላቸው ድጋፍ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እያሳደጉ መሆኑ ተገለጸ።

በከተማ አስተዳደሩ በምግብ ዋስትናና ሴፍቲኔት ፕሮግራም ተጠቃሚዎች እየለማ ያለ ሰብል ዛሬ ተጎብኝቷል።


ከተጠቃሚዎች መካከል ወይዘሮ አበባ ፍቃዱ በሰጡት አስተያየት፤ በፕሮግራሙ ታቅፈው በተመቻቸላቸው የገቢ ማስገኛ ስራ ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል።


ይህም አካባቢን በማስዋብና ንጽህናን ከመጠበቁ በተጓዳኝ የተሰማሩበት የጓሮ አትክልት ልማት የምግብ ዋስትናቸውን ከማረጋገጥ አልፈው ምርታቸውን ለገበያ በማቅረብ ላይ እንደሆኑ አስረድተዋል።

ልማቱን ከጀመሩበት ካለፈው ዓመት የበጋው ወቅት ወዲህ ድንች፣ ሽንኩርትና ሌሎችንም አትክልቶችን በማልማት በሚያገኙት ገቢ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እያሳደጉ መሆኑን ገልጸዋል።

በክረምቱ ወራትም ስንዴን ማልማታቸውንና ሰብሉ በጥሩ ቁመና ላይ እንደሚገኝ አንስተዋል።

ሌላው የፕሮግራሙ ተጠቃሚ አቶ ጀማል ሰይድ፤ በአካባቢያቸው ጥቅም ላይ ያልዋለ መሬት ተሰጥቷቸው በማልማት ኢኮኖሚያዊ አቅማቸውን በማሳደግ ተጠቃሚ እንደሆኑ ተናግረዋል።


በከተማዋ በፕሮግራሙ የታቀፉ ከ3 ሺህ 490 በላይ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ወገኖች በተለያዩ የልማት ስራዎች ላይ መሰማራታቸውን የገለጹት ደግሞ የኮምቦልቻ ከተማ ምግብ ዋስትናና ሴፍቲኔት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ እታፈራሁ አሰግደው ናቸው።


የፕሮግራሙ ተጠቃሚዎች በአካባቢ ጽዳት በመሳተፍ ከሚያገኙት ወርሃዊ ገቢ በተጨማሪ ብድር በማመቻቸት በግብርና፣ በግንባታና ሌሎች ልማቶች በመሰማራት ተጨማሪ ጥሪት እንዲያፈሩ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

ከዚህ ውስጥም ከ2 ሺህ በላይ የሚሆኑት በከተማ ግብርና በመሳተፍ በዓመት እስከ ሶስት ጊዜ እያመረቱ በምግብ ራሳቸውን ከመቻል ባለፈ ትርፍ ምርታቸውን ለገበያ እያቀረቡ መሆኑን አስረድተዋል።

የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ወንድወሰን ልሳነወርቅ በበኩላቸው፤ በከተማው በፕሮግራሙ የታቀፉ ወገኖች ጥቅም ላይ ያልዋለ መሬት አልምተው እንዲጠቀሙ በማመቻቸት ውጤታማ መሆናቸውን አብራርተዋል።


በጉብኝቱ ላይ አመራሮች፣ የፕሮግራሙ ተጠቃሚዎችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025