🔇Unmute
አዳማ ፤ጥቅምት 6/2018 (ኢዜአ)፡-በበጀት ዓመቱ 11 ሚሊዮን የዓሣ ጫጩቶችን በማሰራጨት የአርሶ አደሩን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ ትኩረት መሰጠቱን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ።
የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሣ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት የሌማት ትሩፋት ፕሮግራምን በማጠናከር የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና ስርዓተ ምግብን እውን ለማድረግ ወደ ተግባር ተገብቷል።
በዚህም ትኩረት ከተሰጣቸው ዘርፎች አንዱ የዓሣ እርባታ ሥራ መሆኑን ገልጸው፣ ሥራው በሰው ሠራሽና በተፈጥሮ ሐይቆች እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህም በበጀት ዓመቱ 11 ሚሊዮን የዓሣ ጫጩቶችን በማሰራጨት 320 ሺህ ቶን አሣ ለማምረት ግብ መጣሉን ተናግረዋል።

ዕቅዱን ለማሳካት የአሣ ጫጩት ማስፋፊያ ማዕከላት በሁሉም የሀገሪቱ ክልሎች እየተገነቡ መሆናቸውን የገለጹት ሚኒስትር ዴኤታው፣ ሙቀትና ቅዝቃዜን የሚቆጣጠር ዘመናዊ የአሣ ጫጩት ማመላለሻ ማሽኖች ለክልሎች መሰራጨታቸውን ተናግረዋል።
የንጋት ሐይቅን ጨምሮ በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ሐይቆች እንዲሁም በአርሶ አደሩ ቀዬ በሚሰሩ ኩሬዎች የአሣ ጫጩቶች የማስገባት ሥራ በስፋት እየተከናወነ መሆኑንም አስታውቀዋል።

ከሐይቆችና ኩሬዎች አሣን በአግባቡ ለመሰብሰብም ዘመናዊ የዓሣ ማስገሪያ መረቦችና ጀልባዎች ለክልሎች እንዲሰራጩ መደረጉን ነው ፍቅሩ (ዶ/ር) የገለጹት።
በዚህም በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ዋስትና እና ሥርዓተ ምግብን ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026