🔇Unmute
አዳማ ፤ጥቅምት 6/2018 (ኢዜአ)፡-በበጀት ዓመቱ 11 ሚሊዮን የዓሣ ጫጩቶችን በማሰራጨት የአርሶ አደሩን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ ትኩረት መሰጠቱን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ።
የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሣ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት የሌማት ትሩፋት ፕሮግራምን በማጠናከር የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና ስርዓተ ምግብን እውን ለማድረግ ወደ ተግባር ተገብቷል።
በዚህም ትኩረት ከተሰጣቸው ዘርፎች አንዱ የዓሣ እርባታ ሥራ መሆኑን ገልጸው፣ ሥራው በሰው ሠራሽና በተፈጥሮ ሐይቆች እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህም በበጀት ዓመቱ 11 ሚሊዮን የዓሣ ጫጩቶችን በማሰራጨት 320 ሺህ ቶን አሣ ለማምረት ግብ መጣሉን ተናግረዋል።

ዕቅዱን ለማሳካት የአሣ ጫጩት ማስፋፊያ ማዕከላት በሁሉም የሀገሪቱ ክልሎች እየተገነቡ መሆናቸውን የገለጹት ሚኒስትር ዴኤታው፣ ሙቀትና ቅዝቃዜን የሚቆጣጠር ዘመናዊ የአሣ ጫጩት ማመላለሻ ማሽኖች ለክልሎች መሰራጨታቸውን ተናግረዋል።
የንጋት ሐይቅን ጨምሮ በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ሐይቆች እንዲሁም በአርሶ አደሩ ቀዬ በሚሰሩ ኩሬዎች የአሣ ጫጩቶች የማስገባት ሥራ በስፋት እየተከናወነ መሆኑንም አስታውቀዋል።

ከሐይቆችና ኩሬዎች አሣን በአግባቡ ለመሰብሰብም ዘመናዊ የዓሣ ማስገሪያ መረቦችና ጀልባዎች ለክልሎች እንዲሰራጩ መደረጉን ነው ፍቅሩ (ዶ/ር) የገለጹት።
በዚህም በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ዋስትና እና ሥርዓተ ምግብን ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026