የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

የዳልጋ ከብት ዝርያን  በማሻሻል የወተትና የስጋ ምርታማነትን ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው 

Oct 17, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

መቱ ፤ጥቅምት 6/2018 (ኢዜአ)፡-በኢሉባቦር ዞን የዳልጋ ከብት ዝርያን በማሻሻል የወተትና የስጋ ምርታማነትን ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት በመከናወን ላይ እንደሚገኙ የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት አስታወቀ።

የጽሕፈት ቤቱ ምክትል ኃላፊ አቶ አወል መሐመድ ፤ እየጨመረ የመጣውን የእንስሳት ውጤቶች ፍላጎት ለማሟላት የእንስሳቱን ዝርያ ማሻሻል ላይ ትኩረት መሰጠቱን ለኢዜአ ተናግረዋል።

ለዚህም በሰው ሰራሽ ዘዴ በማዳቀል የዳልጋ ከብቶችን ዝርያ በማሻሻል የስጋም ሆነ የወተት ምርት በማሳደግ የአርሶ አደሮችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል።

ዝርያቸው ከተሻሻሉ ላሞች በአማካይ ከስምንት እስከ አስር ሊትር ወተት መገኘቱን ጠቅሰው፤ ይህም ውጤት ከተለምዶው ዝርያ ከሶስት እጥፍ በላይ ብልጫ እንዳለው አስረድተዋል።

በሰው ሰራሽ እንስሳት ከተዳቀሉ ላሞቻቸው የተሻለ የወተት ምርት በማግኘት ተጠቃሚ መሆናቸውን የገለጹት ደግሞ በዞኑ የዲዱ ወረዳ አርሶ አደር አለሙ መሸሻ ናቸው።


በዝርያ ማሻሻል ስራው የሚወለዱ ጥጆች የዕድገት ፍጥነትና የገበያ አዋጭነቱ የላቀ በመሆኑ ልማቱ ከቀድሞ ይበልጥ ተጠቃሚ መሆን እንዳስቻላቸው ተናግረዋል።

አርሶ አደር አዛሉ ለሙ ፤ በሰው ሰራሽ ዘዴ በማዳቀል የተወለደን ወይፈን ተንከባክበው በማሳደግ በጥሩ ዋጋ መሸጣቸውን ተናግረዋል።


የእንስሳት ዝርያዎች ማሻሻያው ከልማዳዊው አረባብ ትልቅ ልዩነት በመኖሩ በአጭር ጊዜ የወተትም ሆነ የስጋ ምርት መስጠት እንደሚያስችል አንስተዋል።

አቶ ዕድገት አሰፋ በበኩላቸው፤በሰው ሰራሽ መንገድ ከተሻሻሉ ላሞቻቸው በቀን እስከ ስምንት ሊትር ወተት እያገኙ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ከግብርና ጽሕፈቱ የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው፤ በኢሉባቦር ዞን ባለፉት ሁለት ዓመታት በሰው ሰራሽ የዝርያ ማሻሻል ከ34 ሺ በላይ እንስሳትን ማዳቀል ተችሏል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025