የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በምስራቅ ወለጋ ዞን የጥራት ደረጃውን የጠበቀ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ በትኩረት እየተሰራ ነው

Oct 23, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ነቀምቴ ፤ ጥቅምት 12/2018 (ኢዜአ)፦በምስራቅ ወለጋ ዞን የጥራት ደረጃውን የጠበቀ ቡና አምርቶ ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ የሚያስችሉ ተግባራት በትኩረት እየተከናወኑ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር አስታወቀ።

በዞኑ በቡና ምርት ላይ ተሰማርተው ለሚገኙ ባለሀብቶች እና አርሶ አደሮች በቡና ምርት ጥራት ላይ ያተኮረ ስልጠና ተሰጥቷል።

በዚሁ ወቅት የዞኑ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ደሱ ለሚ እንደገለጹት በዞኑ የሚገኙ ቡና አምራቾች ከባህላዊ የቡና አመራረት ስልት ወጥተው ጥራት ያለው ቡና ማምረት እንዲችሉ የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ ነው።

አምራቾቹ በሚያመርቱት ቡና ለራሳቸውም ሆነ ለአገር የተሻለ ገቢ ማስገኘት እንዲችሉ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደገፈ የአመራረት ስልትን እንዲከተሉ ከግንዛቤ ማሳደግ ጀምሮ እስከ ግብዓት አቅርቦት ድረስ ድጋፎች እየተደረጉ ነው ብለዋል።

በተለይም ከቡና ጥራት ጋር የተያያዙ ችግሮች በአብዛኛው ከግንዛቤ እጥረት ጋር የሚያያዙ መሆኑን ጠቅሰው ችግሩን ለመፍታት ከአምራቹ ጋር በቅርበት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

ከዚህ ጎን ለጎንም የቡናን ጥራት ማስጠበቅ ላይ ተግዳሮት እየሆነ የሚገኘውን ህገወጥ የቡና ንግድን ለመከላከል ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅርበት እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።

የዞኑ ግብርና ፅህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ ደረጄ ብርሀኑ (ዶ/ር) በበኩላቸው በዞኑ ከ342 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በቡና እየለማ ይገኛል።


ባለፈው ዓመት ከዞኑ 119 ቶን ቡና ለማዕከላዊ ገበያ የቀረበ ሲሆን በዘንድሮው የምርት ዘመንም ወደ 292 ቶን ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ ርብርብ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።

ለማዕከላዊ ገበያ የሚቀርበው ቡና የጥራት ደረጃውን የጠበቀ እንዲሆን ከቡና አምራች ባለሀብቶች እና አርሶ አደሮች ጋር በቅርበት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

የተሰጠው ስልጠናም በቡና ምርት ላይ የሚያጋጥሙ ችግሮችን መለየት፣ ደረጃውን የጠበቀ እና ለቡና ገበያ ተፈላጊ ምርት ማቅረብ እንዲሁም የቡና ብክነትን ለመቀነስ እንደሚረዳም አስረድተዋል።

በስልጠናው ላይ ከተሳተፉ ቡና አምራች አርሶ አደሮች መካከል አቶ ዋጂራ ሰንበታ፤ የቡና ጥራት ሲጨምር ገቢን የሚያሳድግ በመሆኑ ለቡና ጥራት ትኩረት መስጠታቸውን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የአፍሪካ የልማትና ትብብር ዓርማ - ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በታዋቂው ታይም መጽሔት ገጽ

አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...

Sep 14, 2026

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026