🔇Unmute
አዲስ አበባ ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ስኬታማ ድርድር በማካሄዷ እስከ አራት ነጥብ አምስት ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር የሚሆን የዕዳ ሽግሽግ ለማስደረግ መቻሏን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እየተካሄደ ነው።
በመደበኛ ስብሰባው ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ መስከረም 26 ቀን 2018 ዓ.ም ለሁለቱ ምክር ቤቶች የጋራ ስብሰባ ያደረጉትን የመክፈቻ ንግግር አስመልክቶ ከምክር ቤቱ አባላት በቀረቡ ጥያቄዎች ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ምላሽና ማብራሪያ እየሰጡ ይገኛል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ምላሽና ማብራሪያቸው እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ ያለባትን ዕዳ ጫና በንጽጽርና በቁጥር ማየት አስፈላጊ ነው።
በአፍሪካ አንደኛ፣ ሁለተኛና ሶስተኛ የሚባሉ ኢኮኖሚዎች ከኢትዮጵያ በብዙ እጥፍ ዕዳ እንዳለባቸው ጠቅሰው፤ የኢትዮጵያ የዕዳ ጫናም ከ23 ቢሊዮን ዶላር እንደማይበለጥና በንጽጽር ሲታይም ያን ያክል አስደንጋጭ እንዳልሆነ አስገንዝበዋል።
የኢትዮጵያ ዕዳ መጥፎ የሆነው የተወሰደበት መንገድ መሆኑን አብራርተው፤ አብዛኛው ብድር በአጭር ጊዜ መክፈል የሚጠይቅ የኮሜርሻል ብድር ሥርዓት ስለሆነ የኢትዮጵያ ጥያቄ መሸጋሸግ አለበት የሚል መሆኑን አንስተዋል።
ኢትዮጵያ ባደረገችው ድርድር ከ4 እስከ 4 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ የእዳ ሽግሽግ እንደተደረገ ጠቁመው፤ ይህም ሪፎርሙ ያስገኘው ታላቅ ድል መሆኑን ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ አሁን ላይ ብድር ለመክፈል ምንም ዓይነት ችግር እንደሌለባት አስታውቀው፤ ለውጡን ተከትሎም መንግስት አንድም ዶላር የኮሜርሻል ብድር እንዳልወሰደ ተናግረዋል።
ከሪፎርሙ በፊት በዚህ ከቀጠለ እንቸገራለን የሚል ስጋት የነበረ ቢሆንም፤ አሁን ላይ ኢትዮጵያ ዕዳ ለማስተዳደር ምንም ዓይነት ችግር እንደሌለባት አስገንዝበዋል።
በምክር ቤቱ መደበኛ ስብሰባ የሀገራት አምባሳደሮች፣ የዓለም አቀፍ ተቋማት ተወካዮች፣ የኃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡
አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...
Sep 14, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026