የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የኢትዮጵያ ስኬታማ ድርድር የዕዳ ሽግሽግ ማስደረግ አስችሏል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

Oct 29, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ስኬታማ ድርድር በማካሄዷ እስከ አራት ነጥብ አምስት ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር የሚሆን የዕዳ ሽግሽግ ለማስደረግ መቻሏን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እየተካሄደ ነው።

በመደበኛ ስብሰባው ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ መስከረም 26 ቀን 2018 ዓ.ም ለሁለቱ ምክር ቤቶች የጋራ ስብሰባ ያደረጉትን የመክፈቻ ንግግር አስመልክቶ ከምክር ቤቱ አባላት በቀረቡ ጥያቄዎች ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ምላሽና ማብራሪያ እየሰጡ ይገኛል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ምላሽና ማብራሪያቸው እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ ያለባትን ዕዳ ጫና በንጽጽርና በቁጥር ማየት አስፈላጊ ነው።

በአፍሪካ አንደኛ፣ ሁለተኛና ሶስተኛ የሚባሉ ኢኮኖሚዎች ከኢትዮጵያ በብዙ እጥፍ ዕዳ እንዳለባቸው ጠቅሰው፤ የኢትዮጵያ የዕዳ ጫናም ከ23 ቢሊዮን ዶላር እንደማይበለጥና በንጽጽር ሲታይም ያን ያክል አስደንጋጭ እንዳልሆነ አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ዕዳ መጥፎ የሆነው የተወሰደበት መንገድ መሆኑን አብራርተው፤ አብዛኛው ብድር በአጭር ጊዜ መክፈል የሚጠይቅ የኮሜርሻል ብድር ሥርዓት ስለሆነ የኢትዮጵያ ጥያቄ መሸጋሸግ አለበት የሚል መሆኑን አንስተዋል።

ኢትዮጵያ ባደረገችው ድርድር ከ4 እስከ 4 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ የእዳ ሽግሽግ እንደተደረገ ጠቁመው፤ ይህም ሪፎርሙ ያስገኘው ታላቅ ድል መሆኑን ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ አሁን ላይ ብድር ለመክፈል ምንም ዓይነት ችግር እንደሌለባት አስታውቀው፤ ለውጡን ተከትሎም መንግስት አንድም ዶላር የኮሜርሻል ብድር እንዳልወሰደ ተናግረዋል።

ከሪፎርሙ በፊት በዚህ ከቀጠለ እንቸገራለን የሚል ስጋት የነበረ ቢሆንም፤ አሁን ላይ ኢትዮጵያ ዕዳ ለማስተዳደር ምንም ዓይነት ችግር እንደሌለባት አስገንዝበዋል።

በምክር ቤቱ መደበኛ ስብሰባ የሀገራት አምባሳደሮች፣ የዓለም አቀፍ ተቋማት ተወካዮች፣ የኃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የአፍሪካ የልማትና ትብብር ዓርማ - ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በታዋቂው ታይም መጽሔት ገጽ

አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...

Sep 14, 2026

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026