🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 19/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ቀይ ባህርን ለማጣት የወሰደባትን 30 ዓመታት ወደ ቀይ ባህር ለመመለስ ሌላ 30 ዓመታት አያስፈልጋትም ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ በተካሀደበት ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሰላምና ጸጥታን በሚመለከት በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ፣ ኢትዮጵያ ቀይ ባህርን ለማጣት የወሰደባትን 30 ዓመታት ወደ ቀይ ባህር ለመመለስ ሌላ 30 ዓመታት አያስፈልጋትም ብለዋል።
የቀይ ባህር ጉዳይ ህጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልክዓ ምድራዊ(ጂኦግራፊያዊ) እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ እንደሆነ እናምናለን ሲሉም ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ቀይ ባህርን ለማጣት 30 ዓመት በላይ ያህል የወሰደ ትግል እንደነበር ያስታወሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ሀገሪቱ ወደ ቀይ ባህር ለመመለስ 30 ዓመት አያስፈልጋትም ነው ያሉት።
ይህን ጉዳይ ለመፍታት በተረጋጋ፣ በሰከነ እና በውይይት መሄድ አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመው፤ ለማጣት የፈጀውን ያህል ለመመለስ አይፈጅብንም ሲሉም በአጽንኦት ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችበት መንገድ የኢትዮጵያ ህዝብም ሆነ ካቢኔ ያልወሰነው፣ ተወካዮች ያላዩት መሆኑን ጠቁመው፤ ጥያቄው ይህን ትልቅ ጉዳይ ማን ወሰነው ብሎ መጠየቅ ተገቢ መሆኑን አስረድተዋል።
ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችበት መንገድ ህጋዊ እና ተቋማዊ መሠረት የሌለው እንደሆነም ነው የገለጹት።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026