የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

ከጥቂት ዓመታት ወዲህ ቡና ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመጠቀም በጥራትና በብዛት እየተመረተ ነው - ባለስልጣኑ

Oct 31, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 20/2018(ኢዜአ)፦ ከጥቂት ዓመታት ወዲህ ከዘልማዳዊ የአመራረት ዘዴ በመውጣት ቡና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በጥራትና በብዛት እየተመረተ መሆኑን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን ገለጸ።

በቡና ምርትና ምርታማነት እንዲሁም ጥራት ላይ እየታየ ያለው ለውጥ የተቀናጀ ሥራ ድምር ውጤት መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች ገልጸዋል።

በዓለም ከፍተኛ ቡና አምራች ተብለው በግንባር ቀደምትነት ከሚጠቀሱ አምስት ሀገራት መካከል ኢትዮጵያ አንዷ ናት።

የኢትዮጵያ ባለ ልዩ ጣዕም ቡና በዓለም ተወዳጅ እና ተፈላጊ ነው።

የኢትዮጵያ ምጣኔ ሃብት የጀርባ አጥንትና የውጭ ምንዛሬ ምንጭ የሆነውን ቡና በብዛትና በጥራት በማምረት ከዘርፉ የበለጠ ተጠቃሚ ለመሆን የተለያዩ ሥራዎች ተጀምረዋል።

መንግሥት ለግብርናው ዘርፍ በተለይም ለቡና ጥራትና ምርታማነት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ ባለው ሥራ ተጨባጭ ውጤቶች እየተገኙ መጥተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ሰሞኑን ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሲሰጡ ይህንኑ አረጋግጠዋል።

እንደ እርሳቸው ገለጻ፣ ከለውጡ ዓመታት ማግስት ኢትዮጵያ በዓመት 4 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታል ቡና ያመረተች ሲሆን ከወጪ ንግዱ 700 ሚሊዮን ዶላር አግኝታለች።

በ2017 በጀት ዓመት 11 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታል ቡና መመረቱን ገልጸው፤ ከወጪ ንግዱም 2 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር መገኘቱን አንስተዋል።

የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ታጋይ ኑሩ ከጥቂት ዓመታት ወዲህ ከዘልማዳዊ የአመራረት ዘዴ በመውጣት ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመጠቀም ቡና በጥራትና በብዛት እየተመረተ ነው ብለዋል።

ቀደም ሲል የተንዛዛ የነበረውን የቡና የግብይት ሥርዓትም በፖሊሲ የተደገፈ ማሻሻያ መደረጉን ገልጸዋል።

በዚህም በቡና ምርትና ምርታማነት ላይ ከመጣው ለውጥ ባለፈ ከወጪ ንግዱ የሚገኘው ገቢ ከፍተኛ እንዲሆን አስችሏል ብለዋል።

በኢትዮጵያ የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም የሚችሉ የተሻሻሉ ዝርያዎችን ከመጠቀም ባለፈ ያረጁትን በዘመናዊ መሳሪያዎች እየተጎነደሉ በአዲስ እየተተኩ መሆኑን ነው የተናገሩት።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡና ማኅበር ምክትል ፕሬዝዳንት ዘሪሁን ቃሚሶ በበኩላቸው፤ ማኅበሩ በቡና አቅርቦት ሰንሰለት ውስጥ ያሉ ተግዳሮቶች እንዲፈቱና የቡና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ለማስቻል መቋቋሙን ተናግረዋል።

ከለውጡ በፊት ቡና ላኪዎችም ሆኑ አቅራቢዎች ከ94% በላይ ቡና አምራች የሆነውን አርሶ አደር በቴክኒክና በዕውቀት የመደገፍ አዝማሚያ እንዳልነበርም አንስተዋል።

ይህም አርሶ አደሩ ቡናን በብዛትና በጥራት እንዳያመርት ከማድረግ ባለፈ ከምርቱ ተገቢውን ጥቅም እንዳያገኝ ማድረጉን ተናግረዋል።

ማኅበሩ የቡና ልማትን ሥራ በጥናትና ምርምር እንዲታገዝ ሥርዓተ ትምህርት ከመቅረጽ ባለፈ ከዘር ዝግጅትና አቅርቦት ጀምሮ ለቡና ጉንደላ የሚሆኑ አስፈላጊ ግብዓቶችን ለአርሶ አደሩ እያከፋፈለ ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025